ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከነገ ረቡዕ ታኅሣሥ 19 ጀምሮ ወደ መቀሌ የመንገደኞች የበረራ አገልግሎት እንደሚጀምር አስታወቀ። የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከተቀሰቀሰበት ጊዜ ጀምሮ ተቋርጦ የቆየው የአውሮፕላን አገልግሎት የሚጀምረው የመቀሌ አውሮፕላን ማረፊያ ለበረራ አገልግሎት ዝግጁ መሆኑ ከታየ በኃላ መሆኑ ተገልጿል።
ለሁለት ዓመታት የዘለቀው እና ለበርካቶች ሞትና መፈናቀል ምክንያት የሆነው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት እንዲቆም በመንግሥት እና በህወሃት መካከል የተፈረመውን የሰላም ስምምነት በአዎንታዊነት እንደሚቀበሉት ትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ገለጹ።
በትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች ይማሩ የነበሩ ወጣቶች ጦርነት ሲቀሰቀስ ህልማቸው ተጨናግፏል። ከሌሎች አካባቢ ወደ ትግራይ አቅንተው በትምህርት ላይ የነበሩት ወደ ትውልድ ቀያቸው ከተመለሱ በኋላ ወደ ሌሎች ተቋማት እስኪመደቡ ድረስ መጠበቅ ነበረባቸው። የዛሬው የከወጣቶች ዓለም መሰናዶ በተማሪዎቹ ህልም፣ ስነ ልቦና እና ትምህርት ላይ ያሳደረውን ጫና ይዳስሳል
በኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት ዓመታት በግጭት የወደሙ ጤና ተቋማትን ምልሶ ለመገንባት ቢያንስ 1.4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የጤና ሚኒስቴር ዐስታወቀ። ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት፤ ከቅርብ ጊዜው የትግራይ ጦርነት በሰላም መቋጨት በኋላ በርካታ የህክምና ተቋማትን ስራ ማስጀመር መቻሉንም አመልክተዋል።