ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
የመንግሥት እርምጃዎች ኢትዮጵያ ልትሸከመው ወደማትችል አለመረጋጋት እንደሚያስገቧት ፓርቲዎች አስጠነቀቁ። የአብን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ እናት ፓርቲና መኢአድ መንግሥት "አፈና" እየፈጸመ ነው ሲሉ ከሰዋል። የመንግሥት ኮምዩንኬንሽ አገልግሎት እንደሚለው ግን የፀጥታ ኃይሎች የሚወስዷቸው እርምጃዎች "ህግ የማስከበር" ዓላማ ያላቸው ናቸው
በዓለማችን በምግብ እጦት በዓመት ከአንድ ሚሊዮን በላይ ህጻናት እንደሚሞቱ ተነገረ። የተባበሩት መንግሥታት የህጻናት መርጃ ድርጅት «ዩኒሴፍ» ዛሬ ይፋ ባደረገዉ መረጃ በአሁኑ ወቅት በዓለማችን ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ፤ ወደ 45 ሚሊዮን ህጻናት በረሃብ እየተሰቃዩ ነዉ።
ማሊ ጂሃዲስቶችን ከሚዋጋው (G5) ከሚታወቀዉ የሳህል ሀገራት ጥምረት እና የዓለም አቀፍ ጥምር ጦር ኃይል ቡድን ራስዋን ማግለልዋን ገለፀች። እንደ ጎርጎረሳዉያኑ አቆጣጠር በ 2014 ዓ.ም ማሊ ሞሪታንያ፤ ቡርኪናፋሶ፤ ኒጀር እና ቻድ ተባብረዉ ጂ 5ን በመመስረት በጎርጎረሳዉያኑ 2017 ዓ.ም ጥምር ጦር ማቋቋማቸዉ ይታወሳል።
ኢትዮ-ቴሌኮም ዓለም የደረሰበትን አምስተኛው ትውልድ ወይም 5ጂ ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት አዲስ አበባ ውስጥ በተመረጡ አምስት ሥፍራዎች ላይ አስጀመረ። አገልግሎቱ የአገርን እድገት በቴክኖሎጂ ለማገዝ ታልሞ የተጀመረ መሆኑን ኩባንያው አስታውቋል።