1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሲዳማ አስተዳደር የሲአን መስራች አስተያየት

ሐሙስ፣ ሐምሌ 11 2011

በ1970 ሲአንን ከአባታቸዉ ከአቶ ወልደአማኑኤል ዱባለ ጋር ሆነዉ የመሰረቱት አቶ ደጀኔ ወልደአማኑኤል እንደሚሉት በአስተዳደሩ ጉዳይ በሲዳሞ ዞን በሚገኙ  አካባቢዎች የሚኖረዉ የየትኛዉም ብሔር ተወላጅ ሐሳቡን በነፃነት የመስጠትና የመወሰን መብቱ ሊከበርለት ይገባል።

https://p.dw.com/p/3MH2n
Aktivisten der ethnischen Gruppe der Sidama in Äthiopien
ምስል DW/D. Wolde

የሲዳማ ጥያቄና የሲአን መስራች ምክር

 

የሲዳማ ዞን  የወደፊት እስተዳደርን ለመወሰን የሚሰጠዉ ድምፅ (ሕዝበ ዉሳኔ) በሲዳማ ዞን የሚኖሩ የሁሉም ብሔረሰብ ተወላጆች የሚሳተፉበት እንጂ የሲዳማ ሕዝብ ብቻዉን የሚወስንበት እንደማይሆን ከሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) መስራቾች አንዱ አስታወቁ። በ1970 ሲአንን ከአባታቸዉ ከአቶ ወልደአማኑኤል ዱባለ ጋር ሆነዉ የመሰረቱት አቶ ደጀኔ ወልደአማኑኤል እንደሚሉት በአስተዳደሩ ጉዳይ በሲዳሞ ዞን በሚገኙ  አካባቢዎች የሚኖረዉ የየትኛዉም ብሔር ተወላጅ ሐሳቡን በነፃነት የመስጠትና የመወሰን መብቱ ሊከበርለት ይገባል። የሲዳማ ሕዝብ የወደፊት አስተዳደሩን ለመወሰን ሕዝበ ዉሳኔ መደረግ የነበረበት እስከ ዛሬ ነበር ብለዉ የሚያምኑ የሲዳማ ተወላጆች ግን ዛሬ ከፀጥታ አስከባሪዎችና ከሌሎች ብሔር ተወላጆች ጋር እየተጋጩ ነዉ። ስዊትዘርላንድ የሚኖሩት አቶ ደጀኔ እንደሚሉት ግን ሰዎች ከሌላ አካባቢ መጥተዋልና «አያገባችሁም» ሊባሉ አይገባም። አቶ ደጀኔን ነጋሽ መሐመድ በስልክ አነጋግሯቸዋል።

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ