ግንቦት ሃያና የጠቅላይ ሚንስትሩ መልዕክት
ረቡዕ፣ ግንቦት 20 2006ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራዊያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) የቀድሞዉን የኢትዮጵያ (የደርግን) መንግሥት በነፍጥ ዉጊያ አስወግዶ ሥልጣን የያዘበት 23ኛ ዓመት ኢትዮጵያ ዉስጥ በተለያዩ ሥርዓቶች ሲከበር ነዉ የሰነበተዉ።የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ሐይለ ማርያም ደሰለኝ ዛሬ አዲስ አበባ ስታዲዮም በተከበረዉ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር «አሸባሪ» ያሏቸዉን ግንቦት ሰባት፤ኦነግ፤ ኦብነግንና የኤርትራ መንግሥትን አዉግዘዋል።በሚቀጥለዉ ዓመት ሊደረግ የታቀደዉ ምርጫ ሠላማዊ፤ ፍትሐዊ እና ነፃ ለማድረግም መንግሥታቸዉ እንደሚጥር አስታዉቀዋል።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ዮሕንስ ገብረ እግዚአብሔር የላከልን ዘገባ አለ።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ