1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ድሬደዋን ነፃ የንግድ ቀጠና የሚያደርገው አዲስ አሰራር

ሰኞ፣ ነሐሴ 2 2014

ድሬደዋን ነፃ የንግድ ቀጠና የሚያደርገውን አዲስ አሰራር ለመተግበር ዝግጅት ማጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል። ለተለያዩ መስኮች የቀረጥ ነፃን ጨምሮ የተለያዩ ምቹ ሁኔታዎችን የሚፈቅደው አዲሱ አስራር በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት ተብሏል።

https://p.dw.com/p/4FGXf
Dire Dawa Industrial Park
ምስል Messay Teklu/DW

የድሬ ዳዋ ከተማ በአዲስ አሰራር የነጻ ንግድ ቀጠና ልትሆን ነው

 

ድሬደዋን ነፃ የንግድ ቀጠና የሚያደርገውን አዲስ አሰራር ለመተግበር ዝግጅት ማጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል። ለተለያዩ መስኮች የቀረጥ ነፃን ጨምሮ የተለያዩ ምቹ ሁኔታዎችን የሚፈቅደው አዲሱ አሰራር በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት ተብሏል።

በኢንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የስትራቴጂክ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ኪያ ተካልኝ በቅርብ ቀናት በይፋ ይጀመራል ላሉት የድሬደዋ ነፃ ንግድ ቀጠና አሰራር ትግበራ ዝግጅት አጠናቀናል ብለዋል።

በሀገሪቱ የመጀመርያ የተባለው እና በድሬደዋ የሚተገበረው ነፃ የንግድ ቀጠና አሰራር  በኢንቨስትመንት መስክ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች ምን የተለየ ፋይዳ ያመጣል ለሚለው ጥያቄ አቶ ኪያ ምላሽ ሰጥተዋል።

Kiya Tekalegn, Consultant of Ethiopian Industrial Parks Development Corporation
ምስል Messay Teklu/DW

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የስትራቴጂ አማካሪው አቶ ኪያ በቅርብ ጊዜ ወደ ተግባር ይሸጋገራል ያሉት የድሬደዋ ነፃ የንግድ ቀጠና የተለያዩ ጠቀሜታዎች እንዳሉት አስረድተዋል።

በሀገሪቱ የኢንዱስትሪ እድገት የቀደመ ፋና ወጊነቷን ያጣችው ድሬደዋ ዳግም ለኢንደስትሪው ዘርፍ ማደግ ተስፋ ለተጣለበት አዲስ አሰራር ትግበራ ታጭታለች - አማካሪው እንደሚሉት ድሬደዋ የተመረጠችው በተዘጋጀ መስፈርት ነው።

Dire Dawa Industrial Park
ምስል Messay Teklu/DW

ከሁለት ዓመት በፊት ተመርቆ ስራ የጀመረው የድሬደዋ የኢንዱስትሪያል ፓርክ በውስጡ አስራ አምስት ሼዶች ቤኖረውም በኢንቨስተሮች ተይዞ ወደ ስራ የገባው ከአምስት አይበልጥም። በአጭር ጊዜ ይተገበራል የተባለው አሰራር በእዚህ ረገድ ጥሩ መነቃቃት ይፈጥራል የሚል ተስፋ አሳድራል።

መሳይ ተክሉ

ታምራት ዲንሳ

እሸቴ በቀለ