1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ደቡብ ሱዳን ወደ ጦርነት አዘቅት ትገባ ይሆን? 

ሐሙስ፣ ጥቅምት 27 2012

የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር እና የእስካሁኑ አማፂ ቡድን መሪ ሪያክ ማቻር ከዚሕ ቀደም የተፈራረሙትን የሰላም ዉል ገቢር በማድረግ የአንድነት መንግሥት መመስረት ቁርጠኝነት ባለማሳየታቸዉ ሃገሪቱ እጦርነት አፋፍ ላይ መሆንዋ እየተነገረ ነዉ።

https://p.dw.com/p/3SdmL
Sudan, Khartoum: 
Präsident des Südsudan Salva Kiir Mayarditund Oppositionsführer des Südsudan Riek Machar
ምስል picture-alliance/M. Hjaj

«ቋሚ ኮሚቴው የሚኒስቴሩን የሦስት ወራት ሥራ ገምግሟል»

ሁለቱ ተቀናቃኝ ወገኖች ባለፈው መስከረም ወር ባካሄዱት ውይይት መሠረት ማቻር ወደ አንድነት መንግሥቱ የፊታችን ኅዳር 2 ቀን 2012 ዓ.ም እንዲገቡ ከስምምነት ተደርሶ የነበረ ቢሆንም ባለፉት ሳምንታት ዉስጥ  የደቡብ ሱዳን መንግሥት ዋነኛ ተቃዋሚ አካል ሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት የሰላም ውሉን ተግባራዊ ማድረግ ባለመቻሉ የአንድነት መንግሥት ምሥረታው እንዲዘገይ መጠየቁ ይታወሳል። የአማፂው ወገን መሪ ሪየክ ማቻር ቃል አቀባይ ባለፈዉ ሳምንት ባቀረቡት ጥያቄ፤ ማቻር የአንድነት መንግሥት ምሥረታው ለስድስት ወራት እንዲዘገይ ጠይቀዋል ነበር ያለዉ። ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር በበኩላቸዉ ማቻር ላቀረቡት የይራዘም ጥያቄ በቀጥታ ምላሽ ባይሰጡም፣ በተጠቀሰው ቀን ሁሉም ወገኖች የአንድነት መንግሥቱን ለመመሥረት ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዉ ነበር። ሁለቱ ተቀናቃኝ ወገኖች የስልጣን ዉዝግብ ከገቡበት ከዛሬ አምስት ዓመት ጀምሮ በደቡብ ሱዳን በተቀሰቀሰ የእርስ በርስ ጦርነት እስካሁን ወደ 400 ሺህ የደቡብ ሱዳን ዜጎች ሞተዋል። ዝርዝሩን የብራስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴ አዘጋጅቶታል። በእርስ በርስ ጦርነት ዉስጥ የተዘፈቀችዉ ደቡብ ሱዳን ወደ ባሰ የጦርነት አዘቅት እየተንሸራተተች ነዉ ሲል  በዓለም አቀፍ ደረጃ የግጭትና ቀዉስን መነሻ የሚያጠናዉ ድርጅት «ኢንተርናሽናል ክራይስ ግሩፕ» ማስጠንቀቁ ይታወሳል። ዓለም አቀፉ የቀዉስ እና ግጭት አጥኚ ቡድን ይህን መግለጫ ያወጣዉ የደቡብ ሱዳን ተቃዋሚ ቡድን የአንድነት ምስረታ ቀጠሮዉን ማራዘሙን ተከትሎ ነዉ። 


ገበያዉ ንጉሴ 
አዜብ ታደሰ 
ነጋሽ መሃመድ