የ2016 የአዉሮጳ ሻምፕዮና ነፀብራቅ በኢትዮጵያ
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
በአዲስ አበባ የሚገኘዉ የጀርመን ኤንባሲ የአዉሮጳ ኅብረት ልዑካን እንዲሁም አምስት ምዕራባዉያን ኤንባሲዮች ከኢትዮጵያ የእግር ኳስ ፊደሬሽን ጋር በመተባበር የ 2016 የአዉሮጳ የእግር ኳስ ሻንፕዮና ግጥሚያ ቅድሜ ሰኔ 4 ቀን አዲስ አበባ ላይ አዘጋጅተዋል። ከሰኔ 3 እስከ ሐምሌ 3 ቀን ድረስ የሚዘልቀዉና ፈረንሳይ ዉስጥ የሚካሄደዉ የአዉሮጳ የእግር ኳስ ሻንፕዮና ነፀ-ብራቅ ነዉ በሚል በአዲስ አበባ ስቴዲየም ለአንድ ቀን በተካሄደዉ የእግር ኳስ ግጥምያ የተለያዩ የአዉሮጳ ሃገራትን ወክለዉ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተመረጡ ታዳጊ ሕጻናት ተጫዉተዋል።
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
አዲስ አበባ በሚገኘዉ ስቴዲዮም በተዘጋጀዉ የእግር ኳስ ጨዋታ የተለያዩ የአዉሮጳ ሃገራትንና አዉስትራልያን ወክለዉ የተጋጠሙት ወጣት የእግር ኳስ ቡድኖች የተዉጣጡት በአዲስ አበባ ከሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ቤቶች ሲሆን የተመረጡትም በኤንባሲዎቹ ነበር።
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
በአዲስ አበባ ስቴድዮም በነበረዉ የእግር ኳስ ግጥምያ ከ200 በላይ ተጫዋቾች የተሳተፉበት ሲሆን የጨዋታዉ ተመልካቾች በዕለቱ ዝግጅት መደሰታቸዉ ተመልክቶአል።
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
የ2016 የአዉሮጳ ሻንፕዮና ነፀ-ብራቅ ነዉ በተባለለት እና በአዲስ አበባ ስቴድየም በተካሄደዉ የእግር ኳስ ግጥምያ ላይ የተሳረፉት 15 ዓመትና ከዚያ በታች ዕድሜ ክልል የሚገኙ ታዳጊ ሕጻናት ነበሩ።
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
ጀርመንን ወክለዉ በግጥምያዉ የተሳተፉት አዲስ አበባ ከሚገኘዉ የጀርመን ትምህርት ቤት የተዉጣጡ ተማሪዎች ሲሆኑ የተጋጠሙትም ከኔዘርላንድ የእግር ኳስ ቡድን ጋር ነዉ።
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
የፈረንሳይን ቡድን ወክለዉ የተጋጠሙት ወጣቶች የተዉጣጡት አዲስ አበባ ከሚገኘዉ ከሊሴ ገብረ ማርያም ትምህርት ቤት ነበር።
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
በአዲስ አበባ በተዘጋጀዉ የዘንድሮ የአዉሮጳ ሻንፕዮና ግጥምያ ላይ የተሳተፉት ወጣቶች ሰባት የአዉሮጳ ኅብረት ሃገራትን ወከሉ ሲሆን በእንግድነት አዉስትራልያም ተሳታፊ ነበረች። አዉስትራልያን ወክለዉ የተጋጠሙት ከቅዱስ ያሬድ ትምህርት ቤት የተዉጣጡ ታዳጊ ወጣቶች ነበሩ። በግጥምያዉ የአዉስትራልያ ቡድንን የወከሉት የቅዱስ ያሬድ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ዉድድሩን በአራተኛነት አጠናቀዋል።
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
አዲስ አበባ የሚገኘዉ የጀርመን ኤንባሲ ከዲፕሎማሲ ሥራዉ ባሻገር ከኅብረተሰቡ ጋር በቅርበት ለመገናኘት በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ዝግጅቶችን በማዘጋጀትና እንዲሁም በዝግጅቱ በመካፈል ይታወቃል። ዘንድሮ የተዘጋጀዉ የአዉሮጳ እግር ኳስ ሻንፕዮና ነፀ-ብራቅ የእግር ኳስ ጨዋታም ከዚህ ዓላማ አንዱ መሆኑ ተገልጿል።
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
ባለፈዉ ዓመት ሁለቱ ጀርመኖች የተዋሃዱበት ቀን ሲያከብሩ አዲስ አበባ የሚገኘዉ ኤንባሲ ባዘጋጀዉ መድረክ ወደ ሦስት ሺህ የሚሆኑ ወጣቶችና ሕጻናት ተካፋይ ነበሩ።
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
አየርላንድን በመወከል የተጫወቱት ታዳጊ ሕጻናት የፍቅርና ሰላም ትምህርት ቤት ተማሪዎች ናቸዉ። በግጥምያዉ ቡድን A ኔዘርላንድን ወክለዉ ያሸነፉት የሳሕለ ሥላሴ ቡድን ተጋጣሚዎች ሲሆኑ፤ ፈረንሳይን የወከሉት የሊሴ ገብረማርያም ት/ቤት ተማሪዎች በግጥምያዉ በሁለተኛ ደረጃነት ነዉ ያጠናቀቁት።
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
በግጥምያዉ በእንግድነት የተሰሳተፈዉ የአዉስትራልያ ቡድንን የወከሉት የቅዱስ ያሬድ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ዉድድሩን በአራተኛነት አጠናቀዋል።
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
ጀርመንን የወከሉት የጀርመን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ዉድድሩን በሦስተኛነት ነዉ ያጠናቀቁት። በቡድን B የተሰለፉት ከተለያዩ ትምህርት ቤት የተዉጣጡ ተጋጣሚዎች ለአየርላንድ ቡድን የተሰለፉ ነበሩ። ኢጣልያን ወክለዉ የተጫወቱት የኢጣልያ ትምህርት ቤት ተጋጣሚዎች ናቸዉ። ቼክ ሪፐብሊክን ፤ የአዲስ ዘመን ትምህርት ቤት ተማሪዎች እንዲሁም ለዴንማርክ የጀርመን ቤተ-ክርስትያን ትምህርት ቤት ተማሪዎች በግጥሚያዉ ተሳትፈዋል። ለግማሽ ፍጻሜ ኔዘርላንድ ከኢጣልያ፤ አየርላንድ ከፈረንሳይ ተጋጥመዉ፤ ፈረንሳይና ኔዘርላንድ ከየምድቡ አሸንፈዉ ለዋንጫ ግጥምያ ደርሰዋል።
የአዉሮጳ እግር ኳስ ግጥምያ በአዲስ አበባ
ለዋንጫ ግጥምያ የደረሱት የነዚህ ሁለቱ ሃገራት ተጋጣሚዎች ከፍተኛ ጨዋታን አሳይተዉ ኔዘርላንድ ፈረንሳይን ሁለት ለባዶ በመርታት የዋንጫዉ ባለቤት ሆናለች። በአዲስ አበባ ስቴድየም ለአንድ ቀን የተካሄደዉ የ2016 የአዉሮጳ እግር ኳስ ሻንፕዮና ጨዋታ ነፀ-ብራቅ ግጥምያ ጠንካራ ፉክክር የታየበት ነበር። ምርጥ የሴት እግር ኳስ ተጫዋች ከኔዘርላንድ፤ የወንድ ጠንካራ ተጫዋች ደግሞ ፈረንሳይን ወክለዉ ከተጫወቱ ወጣቶች ተመርጠዋል። በርካታ ግቦችን በማስቆጠር ለኔዘርላንድ የተጫወተዉ ወጣት፤ ምርጥ በረኛ ደግሞ ኢጣልያን ወክሎ በግጥምያዉ ላይ የተሳተፈ ወጣት በመሆን ተመርጧል።