የ2007 የኢትዮጵያ ምርጫ ሂደት ውጤትና የወደፊቱ ጉዞ
እሑድ፣ ግንቦት 23 2007ማስታወቂያ
5ተኛው የኢትዮጵያ አገር አቀፍ ምርጫ ሂደትና ውጤት እንደቀደሙት ምርጫዎች እያነጋገረ ነው ።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከትናንት በስተያ እንዳሳወቀው ገዥው ፓርቲ ኢህአዲግ በመጀመሪያው ደረጃ ውጤት መሠረት አብዛኛውን የፓርላማ መቀመጫ አግኝቷል ። ሙሉው ውጤት ባይነገርም በአሁኑ ምርጫ ተቃዋሚዎች ካለፈውም ምርጫ በባሰ ሁኔታ የተሸነፉ ይመስላል ። በምርጫው ከተሳተፉት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ዋና ዋና የሚባሉት የምርጫውን ውጤትም ሆነ ሂደት እንደማይቀበሉት አስታውቀዋል ።የአፍሪቃ ህብረት ብቻ በውጭ ታዛቢነት የተካፈለበት የእሁዱ ብሔራዊ ምርጫ ሰላማዊ መሆኑ ቢነገርም ተቃዋሚዎች ፍትሃዊም ሰላማዊም አልነበረም ብለዋል ።የየ2007 ዓም የኢትዮጵያ ምርጫ ሂደት ውጤትና የወደፊት ጉዞ በመጪው እሁድ የሚተላለፈው እንወያይ ርዕስ ነው ።
ኂሩት መለሰ
ማንተፍቶት ስለሺ