የፍራንስ ኧሮ ሜዲተራኔ ማህበር ሽልማት ለ«ግራር አካሲያ» ድርጅት24 ኅዳር 2005ሰኞ፣ ኅዳር 24 2005በፈረንሣይ ሀገር ኢትዮጵያን የማስተዋወቅ ስራ የሚያከናውነው « ግራር አካሲያ » የተባለው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት መሥራች ወይዘሮ ህብረት መአሾ የፍራንስ ኧሮ ሜዲተራኔ ማህበርhttps://p.dw.com/p/16uv7ማስታወቂያ በያመቱ ውጤታማ ለሆኑ በፈረንሣይ ለሚኖሩ የውጭ ተወላጅ የሆኑ ሴቶች የሚሰጠው ሽልማት ባለቤት ሆነ። ወይዘሮ ህብረት መአሾ ያቋቋሙት ይኸው ድርጅት በደቡብ ኢትዮጵያ ሀመር ባና ወረዳ ላይ ያካባቢው ነዋሪ ከቱሪዝም ተጠቃሚ የሚሆንበትን ዕቅድ ነድፎም እንደሚንቀሳቀስ የፓሪስዋ ወኪላችን ሀይማኖት ጥሩነህ የላከችልን ዘገባ ያመለክታል። ሃይማኖት ጥሩነህ አርያም ተክሌ ሸዋዬ ለገሰ