የግብፅ የለውጥ እንቅሥቃሤና ውጤቱ ፣
ማክሰኞ፣ ሰኔ 26 2004ማስታወቂያ
ህዝብ ፤ መሠረታዊ መብቶችን ፤ ነጻነትን፣ ፍትኅንና ርትእን ፣ የሥራ ዕድልን ፤ የኑሮ መሻሻልን የሚመለከቱ ጥያቄዎችን አንግቦ ነበረ ፣ የተንቀሣቀሰው። የለውጥ ነፋስ ፣ እንደ ሰደድ እሳት ባቀጣጠለው ፣ የለውጥ ዘመቻ፤ በተለይ ወጣቱ ትውልድ፣ በዘመናዊ የማኅበራዊ መገናኛ መሳሪያዎች ረዳትነት፤ በጽናት ታገለ። ታህሪር አደባባይ ፣ ልክ እንደ ስሙ በትክክል የነጻነት አደባባይ፣ መሆን አለበትም አለ። ግፊቱን በማጠናከርና መስዋእትነትም በመክፈል፤ አምባገነኑን መሪ ከሥልጣን አስወገደ። ሆኖም ፤ አስተዳደሩን በሞግዚትነት ከሚቆጣጠረው የጦር ኃይሉ ም/ቤት ተጽእኖ፣ ሥልጣኑን በእርግጥ ፈልቅቆ ለሲቭል አስተዳደር ማስረከብ ተችሏል? የሚቻልስ ነው ወይ? በግብፅ ፣ የአስተዳደር ለውጥ፤--መነሻው፤ ሂደቱና አስተምህሮቱ፤ የዛሬው የውይይት መድረክ ርእሳችን ነው።
ተክሌ የኋላ
ሒሩት መለሰ