1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የግብፅ የለውጥ እንቅሥቃሤና ውጤቱ ፣

ማክሰኞ፣ ሰኔ 26 2004

የለውጡ እንቅሥቃሤ፣ የግራ፤ የቀኝ ፤ አብዮታዊ ፣ ወግ አጥባቂ ተብሎ፣ በርእዮት የሚመደብ አልነበረም። ንጉሥ የማይባል ፣ ግን፤ ንጉሥ መሰል ፣ 30 ዓመት በመንበር ላይ የተቀመጠ ፣ የአንድ ሰው ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ አስመርሮት የነበረው

https://p.dw.com/p/15QRO

ህዝብ ፤ መሠረታዊ መብቶችን ፤ ነጻነትን፣ ፍትኅንና ርትእን ፣ የሥራ ዕድልን ፤ የኑሮ መሻሻልን የሚመለከቱ ጥያቄዎችን አንግቦ ነበረ ፣ የተንቀሣቀሰው። የለውጥ ነፋስ ፣ እንደ ሰደድ እሳት ባቀጣጠለው ፣ የለውጥ ዘመቻ፤ በተለይ ወጣቱ ትውልድ፣ በዘመናዊ የማኅበራዊ መገናኛ መሳሪያዎች ረዳትነት፤ በጽናት ታገለ። ታህሪር አደባባይ ፣ ልክ እንደ ስሙ በትክክል የነጻነት አደባባይ፣ መሆን አለበትም አለ። ግፊቱን በማጠናከርና መስዋእትነትም በመክፈል፤ አምባገነኑን መሪ ከሥልጣን አስወገደ። ሆኖም ፤ አስተዳደሩን በሞግዚትነት ከሚቆጣጠረው የጦር ኃይሉ ም/ቤት ተጽእኖ፣ ሥልጣኑን በእርግጥ ፈልቅቆ ለሲቭል አስተዳደር ማስረከብ ተችሏል? የሚቻልስ ነው ወይ? በግብፅ ፣ የአስተዳደር ለውጥ፤--መነሻው፤ ሂደቱና አስተምህሮቱ፤ የዛሬው የውይይት መድረክ ርእሳችን ነው።

ተክሌ የኋላ

ሒሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ