1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የግሪክ ጠ/ሚ የበርሊን ጉብኝት

ሰኞ፣ መጋቢት 14 2007

የግሪክ ጠቅላይ ሚኒስትር አሌክሲስ ሲፕራስ ከጥቂት ሰዓታቶች በፊት ጀርመን መዲና በርሊን ላይ ይፋዊ ጉብኝታቸዉን ጀምረዋል።

https://p.dw.com/p/1Evox
Berlin Merkel empfängt Tsipras
ምስል Reuters/H. Hanschke

የጀርመንዋ መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ለአዲሱ የግሪክ ጠቅላይ ሚኒስትር በደማቅ ወታደራዊ አጀብ ነዉ በጽሕፈት ቤታቸዉ አቀባበል ያደረጉላቸዉ። ሲፕራስ የሃገራቸዉ የቁጠባ መረሃ-ግብር የመጀመርያ ረቂቅ ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል። እንዲያም ሆኖ የተባለዉን ቁጠባ ተግባራዊ ለማድረግ ከኅብረቱ ተጨማሪ የገንዘብ ርዳታ እንደሚያስፈልግም አመልክተዋል።

ባለፈዉ ሳምንት የአዉሮጳዉ ሕብረት ሃገራት ተወካዮች ብራስልስ ላይ ባካሄዱት ስብሰባ ግሪክ ከሕብረቱ የገንዘብ ርዳታን ከፈለገች መጀመርያ ሕብረቱ በጠየቃት መሠረት የራስዋን የቁጠባ መረሐ-ግብር ማቅረብ እንዳለባት ዳግም ተናግረዋል። የግሪክ ጠቅላይ ሚኒስትርን የበርሊን ጉብኝትን በተመለከተ ስቱዲዮ ከመግባቴ በፊት ወኪላችን ይልማ ኃይለሚካኤልን አነጋግሬዉ ነበር።

ይልማ ኃይለሚካኤል

አዜብ ታደሰ

ሸዋዩ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ