1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የገና ገበያና የጀርመን ኤኮኖሚ

ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 16 2006

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ ይላሉ ፤ በበዓሉ ለልብስ ገንዘብ ለማውጣት መሳሳት እንደማይገባ ለማስገንዘብ ።

https://p.dw.com/p/1Ago1
Bildergalerie Studenten auf Weihnachtsmarkt
ምስል Getty Images

እዚህ ጀርመን ደግሞ ለገና ያልወጣ ገንዘብ…… የሚል አባባል ባይኖርም ለበዓሉ ብዙ ገንዘብ ማውጣት የተለመደ ነው ። ለስጦታ ፣ ለድግስ ፣ ለአልባሳት ለቤት እቃ ና ለመዝናኛ ብዙ ገንዘብ ከሚፈስባቸው በዓላት ገና ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል ። ባለፈው ህዳርና በመገባደድ ላይ ባለው በታህሳስ ወር ብቻ ጀርመኖች ለገና ገበያ ያወጡት ገንዘብ ከ80 ቢሊዮን ዩሮ ይበልጣል ። ይህም የጀርመንን ኤኮኖሚ በማንቀሳቀስና በመታደግ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለ ሚካኤል ዘግቧል ። ይልማ ከሰሞኑ በየገበያው ተዘዋውሮ የተመለከተውን እንዲሁም የዶቼቬለዎቹ Viktoria Klebe ና Madeleine Meier የዘገቡትን በዛሬው የኤኮኖሚው ዓለም ዝግጅት ያቀርብልናል ።

ይልማ ኃይለ ሚካኤል

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ