1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

«የደድ ባድ» የፍቅር ሃገር

እሑድ፣ የካቲት 11 2010

የ 30 ዓመቱ ሸምሱ ሱልጣን በሳዉዲ ዓረብያ ሲኖር ከአራት ዓመት በላይ ሆነዉ። በልጅነቱ የሃይማኖት ትምህርት ቀስሟል። ጅማ ዩኒቨርስቲ ገብቶ በፋርማሲ ተመርቋል።ሃሳቡን በድምፅም ሆነ በጽሁፍ የመግለጽ አቅሙ ከፍተኛ ነው። ለመድረክ የተፈጠረ እስኪመስል ድረስ መድረክ የመቆጣጠር ችሎታው ከፍተኛ እንደሆነ ብዙዎች ይናገሩለታል።

https://p.dw.com/p/2spfq
Shemsu Sultan - Buch Cover
ምስል privat

በስልጤኛ ቋንቋ የወጣዉ የታሪክና የግጥም መድብል 

የተለያዩ ቋንቋዎችን በመጠቀም በሚያነሳቸው ሃሳቦች ታዳሚውን የመያዝ አቅሙ ከፍተኛ እንደሆነ በመድረክ ላይ ያዩት ይመሰክራሉ።  ሸምሱ የመድረክ ስራዎቹም በአዳራሹ የሚገኙ የተለያዩ ቋንቋ ተናጋሪዎችን ግምት ውስጥ ያስገባ ነው። ዩኒቨርስቲ እያለ በስልጤ ቋንቋ የቀልብ ገርባሻት የተባለ መጽሐፍ አሁን ደግሞ ሪያድ ከመጣ በኋላ የድድ ባድ የተሰኘ መድብል አሳትሟል። ብዙ ጊዜ መድረክ ላይ ሽልማት ይጎርፍለታል። ቀልዶቹ ዝም ብለው ቧልት አይነት አይደሉም ማህበራዊ ህጸጾችን እያወጡ የሚተቹ ናቸው። በዚህ ዝግጅታችን ሸምሱን ሪያድ ላይ በስልክ አግኝተን ስራዉን የሥነ-ፅሑፍና የመድረክ ልምዱን እንዲያጫዉተን ጠይቀነዋል። ሙሉ ቅንብሩን የድምፅ ማድመጫ ማዕቀፉን በመጫን ይከታተሉ።

አዜብ ታደሰ

ልደት አበበ