የደቡብ ሱዳን ድርድር ተስፋና ቀቢፀ-ተስፋ
ረቡዕ፣ መስከረም 21 2007ማስታወቂያ
የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ሐይላት ባሕርዳር-ዉስጥ የሚያደርጉት ድርድር አሁንም በሠላም ተስፋና በቀቢፀ-ተስፋ እንደተቃርጠ መሆኑን የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) አንድ ሐላፊ አስታወቁ።ተፋላሚ ሐይላት የተፈራረሙትን የተኩስ አቁም ዉል ገቢራዊነት የሚቆጣጠረዉና የሚያጣራዉ የኢጋድ ቡድን ሐላፊ አምባሳደር ተፈራ ሻዉል እንዳሉት የባሕርዳሩ ድርድር ጥሩ ተስፋ እየታየበት ነዉ።እዚያዉ ደቡብ ሱዳን ዉስጥም ግጭቱ እየቀዘቀዘ ነዉ።ይሁንና የድርድሩ ሒደትም ሆነ የግጭቱ መቀዛቀዝ፤ አምባሳደሩ እንደሚሉት ለዘላቂ ሠላም ዋስተና ከሚሆኑበት ደረጃ አልደረሱም። አምባሳደር ተፈራን በስልክ አነጋግሬያቸዋለሁ።
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ