1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዩኤስ አብራሪ የለሽ አይሮፕላን ጥቃት

ሐሙስ፣ ግንቦት 30 2004

ዩኤስ አሜሪካ በአብራሪ የለሽ የጦር አይሮፕላን ጥቃት እንደምትሰነዝር የሚያረጋግጡ መረጃዎች ጥቂቶች ናቸው። ምክንያቱም ብዙው መረጃ የመነጨው ማንነታቸው ከማይታወቁ ምንጮች ነው ፣ በአሁኑ ጊዜ ግልጽ የሆነ ጉዳይ ቢኖር ግን ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ሽብርተኝነትን ለመታገል በዚህ የጦር አይሮፕላን መጠቀሙን ማጠናከራቸው ነው።

https://p.dw.com/p/159M5
FILE - In this Jan. 31, 2010 file photo an unmanned U.S. Predator drone flies over Kandahar Air Field, southern Afghanistan, on a moon-lit night. Drones are often called the weapon of choice of the Obama administration, which quadrupled drone strikes against al-Qaida targets in Pakistan's lawless tribal areas, up from less than 50 under the Bush administration to more than 220 in the past three years. (AP Photo/Kirsty Wigglesworth, File)
ምስል picture alliance/dpa

እአአ 2012 ዓም ከገባ ወዲህ እንኳን በፓኪስታንና አፍጋኒስታን ድንበር አካባቢ በዚሁ የጦር አይሮፕላን ቢያንስ ሀያ ጊዜ ጥቃት ተጥሎዋል። በትናንቱ ዕለትም አሜሪካውያኑ የአል ቓይዳ አመራር ሁለተኛ ቦታ ላይ የሚገኙትን አቡ ጃሃጃ ኣል ሊቢንን መግደሉ ተሳክቶላቸዋል። ዩኤስ አሜሪካ ሊቢን ይዞ ለማስረክባት አንድ ሚልዮን ዶላር ለመክፈል ዝግጁ ነበረች። ፓኪስታን ይህንኑ አሸባሪዎች የተባሉትን ብቻ ሳይሆን የሲቭል ሕዝብን ሕይወት ጭምር ያጠፋውን የአሜሪካ ርምጃ ሕገ ወጥ አድርጋ ብትመለከተውም፡ የዶይቸ ቬለ ባልደረባ ዛንድራ ፔተርስማን እንደዘገበችው፡ ዩኤስ አሜሪካ ይህንን ውጤታማ የሆነውን የትግል ሥልቷን ለመለወጥ ፍላጎት የላትም።

አብራሪ በሌለው የጦር አይሮፕላን የሚሰነዘረው የዩኤስ አሜሪካ ጥቃት በፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ የሥልጣን ዘመን በጉልህ ጨምሮዋል። ከአየር የሚሰነዘረውን የግድያ ጥቃት በተመለከተ የመጨረሻውን ውሳኔ የሚሰጡት አሜሪካዊው ፕሬዚደንት ናቸው።
« ይህ አሜሪካውያንን፡ አሜሪካውያን ተቋማትንና የጦር ሰፈሮችን፡ ወዘተ፡ ለመጉዳት የሚሞክሩ አሸባሪዎች ናቸው ተብለው ስማቸው በዝርዝራችን ውስጥ በተጠቀሱ የታወቁ ሰዎች አንጻር ሆን ተብሎ ጥቃት ለመሰንዘር የሚደረግ ጥረት ነው። ስለዚህ ብዙዎቹ እነዚህ ጥቃቶች የተጣሉት የአል ቓይዳ ተዋጊዎች ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች በሚንቀሳቀሱባቸው እና በቀላሉ ሊደረስባቸው በማይችሉት በፓኪስታን እና በአፍጋኒስታን ድንበር መካከል በሚገኙት አካባቢዎች ነው። እነዚህን ግለሰቦች በሌላ መንገድ እንያዝ ካልን ግን ይህ ከኛ አሁን ከምንጠቀምበት የበለጠ ጠንካራ የጦር ርምጃ መውሰድን ይጠይቅብናል። »
የፓኪስታን መንግሥት በማይቆጣጠራቸው የሀገሩ ጎሣዎች በሚኖሩባቸው አካባቢዎች ባለፉት ሁለት ሣምንታት ብቻ በአብራሪ የለሹ የጦር አይሮፕላን ስምንት የሌሊት ጥቃቶች፡ ካለፉት አምስት ወራት ወዲህ ደግሞ ሀያ ጥቃቶጭ ተጥለዋል። ባንድ በኩል ይኸው ዘመናዊው የጦር አይሮፕላን ሮኬቶቹን የሚጥለው በቀላሉ ሊደረስበት በማይችለው በፓኪስታን እና በአፍጋኒስታን ድንበር እንደመሆኑ መጠን፡ በሌላ ወገን ደግሞ፡ አክራሪ ሙሥሊሞች፡ የስለላ ድርጅቶች እና የፓኪስታን ጦር ኃይል ጋዜጠኞች ወዳካባቢው በመሄድ ሁኔታው እንዲዳይዘግቡ ስለሚያከላክሉ የሚያደርሰው ጉዳት በትክክል ይህ ነው ብሎ ለመናገር ይከብዳል። በዚህም የተነሳ የጥቃቱን በተመለከተ መረጃ የሚገኘው ከስለላ ድርጅት ጋ ግንኙነት ካላቸው ምንጮች፡ ማንነታቸው ካልታወቁ የመንግሥት ምንጮች እና የጎሣ አባላት፣ መረጃው ሀቅ ወይም ፕሮፓጋንዳ ይሁን አይሁን መለየቱ ያዳግታል። በዚያም ሆነ በዚህ ግን የፓኪስታን ጦር ኃይል ይህንኑ የአብራሪ የለሽ የጦር አይሮፕላን ጥቃት እንዲያበቃ ከፍተኛ ግፊት አርፎበታል። ጥቃቱ ከሀገሪቱ ህብረተሰብ ተቃውሞ ተፈራረቆበታል።

ይኸው አሸባሪ የተባሉትን ብቻ ሳይሆን የሲቭል ሕዝብን ሕይወት ጭምር እያጠፋ ያለውን የሁለቱን ሀገሮች ግንኙነትን ይበልጡን እያሻከረው የተገኘው የአብራሪ የለሽ የጦር አይሮፕላን ጥቃት ዓለም አቀፍ ሕግጋትን የሚጥስ መሆኑን የፓኪስታን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሂና ራባኒ ገልጸዋል።
« በኛ አመለካከት በአብራሪ የለሽ የጦር አይሮፕላን የሚጣል ጥቃት በጠቅላላ ሕገ ወጥ ነው። ዓለም አቀፍ ሕግን ይጥሳል። ከሁሉም በላይ ግን ይህን አካባቢ ከአክራሪነትና ከሽብርተኝነት ነፃ ለማድረግ የተጀመረውን ትግል ይጎዳል። በጥቃቱ ዒላማ የሆነ አንድ ተጠርጣሪ ሽብርተኛ ቢገደልም፡ ርምጃው ሌሎች አምስት ወይም አሥር ተከታዮችን በመፍጠር አክራሪነት ይበልጥ ያባባሳል። »

In this Sunday, Dec. 11, 2011 photo, masked Pakistani Taliban militants take part in a training session in an area of Pakistan's tribal South Waziristan region along the Afghan border. Associated Press reporter, photographer and videographer Ishtiaq Mahsud spent six days with fighters from the Pakistani Taliban close to the Afghan border. His account of their travels through South Waziristan offers a glimpse into an area that the Pakistani military claimed had been brought under control following an army offensive two years ago. (AP Photo/Ishtiaq Mahsud)
የአክራሪ ሙሥሊም ማሠልጠኛ ሰፈር በዋዚሪስታን አካባቢምስል AP
ARCHIV - Ein Screenshot des amerikanischen Intel-Center eines Videos, das am 07.10.2009 im Internet veröffentlicht wurde und den El-Kaida-Kommandeurs in Afghanistan, Abu Jahja al-Libi zeigt. Die USA haben einem Medienbericht zufolge versucht, den hohen Al-Kaida-Führer Abu Jahja al-Libi mit einem Drohnenangriff im pakistanischen Grenzgebiet zu Afghanistan zu töten. Wie die «Washington Post» am Dienstag (05.06.2012) online unter Berufung auf amerikanische und pakistanische Regierungsbeamte berichtete, sei aber noch unklar, ob «Al-Kaidas Nummer zwei» bei dem Angriff am Vortag tatsächlich verwundet oder getötet wurde. Foto: Intel-Center (ACHTUNG: Verwendung nur zu redaktionellen Zwecken bei vollständiger Nennung der Quelle: «Foto: Intel-Center» und im Zusammenhang mit der aktuellen Berichterstattung zu «Zeitung: Drohnenangriff in Pakistan galt Al-Kaidas Nummer zwei»; zu dpa «Zeitung: Drohnenangriff in Pakistan galt Al-Kaidas Nummer zwei» vom 05.06.2012) +++(c) dpa - Bildfunk+++
አቡ ጃሃጃ ኣል ሊቢንምስል picture-alliance/dpa

ዛንድራ ፔተርስማን

አርያም ተክሌ

ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ