የወጣቶች መድረክ22 ታኅሣሥ 2003ዓርብ፣ ታኅሣሥ 22 2003በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር መሰረት አሮጌው 2010 ዓ.ም. ተሰናብቶ አዲሱ ዓመት ቤት ለምቦሳ ሊባልለት አንድ ጀምበር ብቻ እንድታዘቀዝቅ ይጠበቃል። እናም የአዲስ ዓመቷ ማለዳ እንደ ሀገራችን የመስከረም ጥቢ አደዩን በመስክ ላይ አፍክታ «እየሆ አበባዬ!» ባይባልላትም፤ አዲስ ተስፋ ግን መሰነቋ አይቀርም።https://p.dw.com/p/QlfLአደይ መሳይ የካሊፎርኒያ አበባምስል Marinella Trovatoማስታወቂያዓመት ዳግም ላይመለስ ምንግዜም በዘመን ጅረት ቁልቁል ይፈሳል። ብዙዎች ታዲያ የሌትና መዓልት እንዲያ በጥድፊያ የመፈራረቁ ነገር የሚያስጨንቃቸውን ያህል፤ ደንታም የማይሰጣቸው አይታጡም። ጊዜ ግን ለጊዜው ድምፁን አጥፍቶ መፍሰሱን የሚያግደው ሀይል የለም።