የኩባ አብዮት 50ኛ አመት ክብረ-በዓል
ዓርብ፣ ታኅሣሥ 24 2001ማስታወቂያ
የኩባ ኮሚንስቶች ሥልጣን የያዙበት 50ኛ አመት በዓል ትናንት ኩባ ዉስጥ በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተከብሮ ዉሏል።ሳንቲያጎ ደ ቡባ በተከበረዉ በአል ላይ ከሰወስት ሺሕ የሚበልጡ ከዉጪና ከሐገር ዉስጥ የተጋበዙ እንግዶች ተገኝተዉ ነበር።አዲሱ የኩባ መሪ ራኡል ካስትሮ ለእንግዶቹ ባደረጉት ንግግር የኩባ ሶሻሊዝም በጠንካራ መሠረት ላይ መጣሉን አዉስተዉ የሐገሪቱ ሕዝብ ወደፊትም ከባድ ጊዜ እንደሚጠብቀዉ አስታዉቀዋል።ሚሻኤል ካስትሪቲዮስ የዘገበዉን ነጋሽ መሐመድ አጠናቅሮታል።