1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የእስራኤል የጋዛ ድብደባ መቆም

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 29 2006

የተኩስ አቁሙ ተግባራዊ ከመሆኑ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት የፍልስጤም ደፈጣ ተዋጊዎች ሮኬቶችን ወደ እስራኤል ተኩሰው ነበር ። ላለፉት 28 ቀናት በተካሄደው ድብደባ ቤታቸው ታስረው የቆዩት ፍልስጤማውያንም ዛሬ መንገዶችንና ገበያዎችን ሞልተው ታይተዋል ።

https://p.dw.com/p/1CpEj
Israel Krieg Gaza Abzug Feuerpause Waffenstillstand 04.08.2014
ምስል GIL COHEN MAGEN/AFP/Getty Images

እስራኤል በጋዛ ለ4 ሳምንታት ያካሄደችውን ድብደባ ዛሬ ጋብ አድርጋ የ72 ሰዓታት የተኩስ አቁም አውጃለች ። የእስራኤል እግረኛ ወታደሮች ዛሬ ጋዛን ለቀው እስራኤል ድንበር ላይ ሰፍረዋል። ሆኖም የእስራኤል ጦር ለሚሰነዘርበት ማናቸውም ጥቃት የአፀፋ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል ። የተኩስ አቁሙ ተግባራዊ ከመሆኑ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት የፍልስጤም ደፈጣ ተዋጊዎች ሮኬቶችን ወደ እስራኤል ተኩሰው ነበር ። ላለፉት 28 ቀናት በተካሄደው ድብደባ ቤታቸው ታስረው የቆዩት ፍልስጤማውያንም ዛሬ መንገዶችንና ገበያዎችን ሞልተው ታይተዋል ። ዛሬ ተግባራዊ ስለሆነው የተኩስ አቁምና ተግባራዊነቱ እንዲሁም ስለ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ የሃይፋውን ወኪላችንን ግርማው አሻግሬን በስልክ አነጋግሬዋለሁ ።

ግርማው አሻግሬ

ሂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ