የኤርትራ ስደተኞች UNHCR እና ኢጣልያ
ረቡዕ፣ ሐምሌ 8 2001ማስታወቂያ
በወቅቱ የስደተኞቹን መርከብ ያስቆመው የኢጣልያ ባህር ኃይል ስደተኞቹን በኃይል ወደ ሊቢያ መርከብ አዛውሮ ወደ ሊቢያ ሲያግዝ ፣ ከመካከላቸው የተወሰኑት መቁሰላቸውና በኢጣልያ ቆይታቸውም ምግብ አለማግኘታቸው ተዘግቧል ። በተጨማሪም እነዚሁ ሰዎች የግል ንብረቶቻቸው እና ሰነዶቻቸውም እንደተወሰደባቸው ተነግረዋል ። እነዚህን መረጃዎች ከስደተኞቹ ያገኘው UNHCR ከኢጣልያ መንግስት ማብራሪያ የሚጠይቅ ደብዳቤ ልኳል ። ወቀሳው የቀረበበት የኢጣልያ መንግስት ክሱን በሙሉ ሀሰት ሲል ለደረሰበት ስም ማጥፋት ይቅርታ ልጠየቅ ይገባል ብሏል ። ተክለ እዝጊ ገብረ እየሱስ ከሮም
ተክለ እዝጊ ገብረ እየሱስ ፣ ሂሩት መለሰ /ሸዋዬ ለገሠ