የኤርትራና የጅቡቲ ዉዝግብና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት
ሐሙስ፣ መጋቢት 24 2001ማስታወቂያ
ኤርትራ በሐይል ይዛዋለች ከሚባለዉ የጅቡቲ ግዛት ለቅቃ-አለመዉጣትዋን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አስታወቁ።ዋና ፀሐፊ ፓን ጊ ሙን ከትናንት በስቲያ ለፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት በፃፉት ደብዳቤ እንዳሉት ኤርትራ የጅቡቲን ግዛት እንድትለቅ ምክር ቤቱ ባለፈዉ ጥር ያሳለፈዉን ዉሳኔ አላከበረችም።የኤርትራ የያዝኩትም የተያዘብኝም ግዛት የለም ባይ ናት።ዋና ፀሐፊ ፓን ጊ ሙን እንደሚሉት ግን የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት በኤርትራ መንግሥት ላይ አስገዳጅ ዉሳኔ ማሳለፍ አለበት።አበበ ፈለቀ ከዋሽንግተን ዲሲ ዝር ዝር ዘገባ ልኮልናል።