1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ጦር ከሑዱር መዉጣቱና አ-ሸባብ

ሐሙስ፣ መጋቢት 12 2005

መሳሳብ።ዉሐ ቅዳ ዉሐ መልስ አይነት።የኢትዮጵያ፥ የሶማሊያ መንግሥት ወይም የአሚሶም ጦር ሲመጣ አሸባብ ይሸሻል።ጦሩ ሲወጣ አሸባብ ይመለሳል።እስከ መቼ? አይታወቅም።ኢትዮጵያ ከሁዱር የወጣችበት ምክንያትም እንደተመልካቹ ይለያይል።

https://p.dw.com/p/182H9
BURAKABA, SOMALIA: Ethiopian soldiers ride an army vehicle on their way to Mogadishu, 28 December 2006. Somali government forces backed by Ethiopian troops, tanks and aircraft were 29 December 2006 poised to take control of the capital Mogadishu, which was calm but tense after a day of gunfire and looting. AFP PHOTO PETER DELARUE (Photo credit should read PETER DELARUE/AFP/Getty Images)
የኢትዮጵያ ጦር-ሶማሊያምስል PETER DELARUE/AFP/Getty Images

ሶማሊያ የዘመተዉ የኢትዮጵያ ጦር የባኮል ክፍለ-ግዛት ዋና ከተማ ሑዱርን ለቅቆ በወጣ በሰዓታት ልዩነት ዉስጥ የሶማሊያዉ አክራሪ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን አ-ሸባብ ከተማይቱን ተቆጣጥሯቷል።አንዳድ ዘገቦች እንደሚጠቁሙት ኢትዮጵያ ጦሯን ከሑዱር ያስወጣችዉ ከሶማሊያ መንግሥትና ከአፍሪቃ ሕብረት ሠራዊት (AMISOM) ጋር ባለመግባባቷ ነዉ።የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ግን «አለመግባባት ተፈጥሯል» የሚለዉን ዘገባ አስልተቀበሉትም። አሸባብ ሑዱርን መቆጣጠሩ ታዛቢዎች እንደሚሉት ማሳሰቡ አልቀረም።

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ እና ጋዜጠኛ መሐመድ ዑመር ባንድ ጉዳይ-አንድ ናቸዉ።አ-ሸባብ ሑዱርን መቆጣጠሩ በጥቅል ሶማሊያ ሠላምና መረጋጋት ላይ የሚያሳድረዉ ተፅዕኖ የለም-በማለት።

ጋዜጠኛ መሐመድ ዑመር ቀጠለ፤

«የኢትዮጵያ ወታደሮች ከሑዱር መዉጣታቸዉና አሸባብ ከተማይቱን መቆጣጠሩ በሶማሊያም ሆነ በመንግሥቷ ላይ የሚያሳድረዉ ተፅዕኖ የለም።ምክንያቱም አሸባቦች ከበርካታ የሶማሊያ ከተሞች ተባርረዋል።እና አሁን በጣም ደካማ ናቸዉ።»

ሌሎች በዚሕ አይስማሙም። አሸባቦችም ሑዱሩን ለመቆጣጠር አልሰነፉም። እንደ ድል አድራጊም እየጨፈሩ ነዉ። «መሸሻቸዉ አይቀርም።» ይላል የሞቅዲሾዉ ጋዜጠኛዉ።

«ባይደዋ የሚገኘዉ የሶማሊያ ጦርና የአፍሪቃ ሕብረት ተባባሪዎቹ ወደ ሑዱር ከተቃረቡ አ-ሸባቦች ከተማይቱን ለቅቀዉ ወደ ጫካ መግባታቸዉ አይቀርም»

«አዲስ ነገር አይደለም።» አሉ አምባሳደሩ።

መሳሳብ። ዉሐ ቅዳ ዉሐ መልስ አይነት።የኢትዮጵያ፥ የሶማሊያ መንግሥት ወይም የአሚሶም ጦር ሲመጣ አሸባብ ይሸሻል።ጦሩ ሲወጣ አሸባብ ይመለሳል።እስከ መቼ? አይታወቅም።ኢትዮጵያ ከሁዱር የወጣችበት ምክንያትም እንደተመልካቹ ይለያይል።

አዣንስ ፍራንስ ፕረስ የጠቀሳቸዉ የአሚሶም ባለሥልጣናት እንደሚሉት ኢትዮጵያ ጦሯን ያስወጣችዉ ጦሯ የሚቆጣጠረዉን አካባቢ አሚሶም እንዲረከበዉ ላቀረበችዉ ጥያቄ አፋጣኝ መልስ ባለመግኘቷ ነዉ።የአዲስ አበበና የሞቃዲሾ መንግሥታት ግንኙነትም በዉጥረት የተሞላ ነዉ ባዮች ናቸዉ፥ የአዣንስ ፍራንስ ፕረስ ምንጮች።

ጋጠኛ መሐመድ ዑመር ደግሞ ከሶማሊያ ባለሥልጣናት ያገኘዉን መረጃ ጠቅሶ እንደሚለዉ ኢትዮጵያ ጦሯን ያስወጣችዉ ለማንም ሳታማክር ነዉ።

«ከአካባቢዉ በደረሰን ዘገባና መረጃ መሠረት ኢትዮጵያ ወታደሮችዋን ከሁዱር እንደምታስወጣ ለከተማይቱም ሆነ ለአካባቢዉ ባለሥልጣናት አላስታወቀችም።ማንንም ሳታስጠነቅቅ ከተማይቱን ለቅቃ ስትወጣ ባካባቢዉ የነበሩት የአሸባብ ተዋጊዎች ወደ ከተማይቱ ገቡ።»

አምባሳደር ዲና በዚሕ አይስማሙ።ጦሩ ሑዱርን የለቀቀዉም ለተለመደ ወታደራዊ ታክቲክ ነዉ ባይ ናቸዉ።የኢትዮጵያ ሶማሊያ የዘመተችበት አለማ አምባሳደር ዲና እንደሚሉት አሁንም አልተቀየረም።

ተልዕኮዉ ለመሳካት አለመሳካቱ ሁሉንም የሚያግባባ መለኪያ የለም።ኢትዮጵያ በራሷ መመዘኛ ተልዕኮዉ ተሳክቷል ብላ፥ በራሷ ጊዜ እንደ ሁዱር ሁሉ ሥልታዊቱን የባይደዋን ከተማ ከለቀቀች ግን ብዙዎች እንደሚሉት ለአሸባብ ታላቅ ድል፥ አሸባብን ለሚወጉት ሐይላት ባንፃሩ ከፍተኛ ዉድቀት ነዉ-የሚሆን።

Ugandan African Union peacekeepers patrol the outskirts of Mogadishu on September 12, 2012. Somalia's president survived an assassination bid today, just two days into his new job, when bomb blasts claimed by Islamist rebels rocked the Mogadishu hotel where he was meeting Kenya's foreign minister. Al-Qaeda linked Shebab insurgents claimed responsibility for Wednesday's attack in which two blasts rocked the hotel where the new president was staying. AFP PHOTO/SIMON MAINA (Photo credit should read SIMON MAINA/AFP/GettyImages)
የአፍሪቃ ሕብረት ጦር-ሞቅዲሽምስል MICHELE SIBILONI/AFP/Getty Images
Policemen walk past the scene of an explosion near the presidential palace in Somalia's capital Mogadishu, March 18, 2013. A car bomb exploded near the presidential palace in the Somali capital Mogadishu on Monday, killing at least 10 people in a blast that appeared to target senior government officials, police said. REUTERS/Feisal Omar (SOMALIA - Tags: CIVIL UNREST CRIME LAW POLITICS)
ሞቅዲሾ-ፍንዳታምስል Reuters

ነጋሽ መሐመድ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ