1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ጤና፤ የመንግስታቸዉ ሁኔታ

ሰኞ፣ ሐምሌ 16 2004

ጠቅላይ ሚንስትሩ ይታከሙበታል የሚባለዉ በብራስልስ-ቤልጂግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኢሜይል የሠጠን መለስ ግን ጠቅላይ ሚንስትሩ ሕክምና ላይ ናቸዉ መባሉን «ሐሰትና ስሕተት» ብሎ ነበር።ዛሬስ-ሐሰት-ስሕተቱ የማን ነዉ? እዉነቱ መለስ ያኔም-ዛሬም መደበኛ ሥራቸዉ ላይ የሉም

https://p.dw.com/p/15dbb
Der aethiopische Ministerpraesident Meles Zenawi, links, und Bundeskanzler Gerhard Schroeder, rechts, unterrichten am Mittwoch, 10. November 2004, in Berlin die Medien ueber ihre Gespraeche. Zenawi haelt sich zu einem dreitaegigen Staatsbesuch in Deutschland auf. (AP Photo/Jockel Finck) ---Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi, left, und German Chancellor Gerhard Schroeder, right, brief the media in Berlin on their talks in the Chancellery, Wednesday, Nov.10, 2004. Zenawi is on a three-day-visit to Germany. (AP Photo/Jockel Finck)
ምስል AP

23 06 12


የኢትዮጵያ ፀጥታ አስከባሪዎች፣ ቤተ እምነቶችን ለማርከሰም ሆነ የእምነት ነፃነት ጠየቅን ያሉ ሙስሊሞችን በአስለቃሽ ጢስ እያፈኑ፣ በዱላ እየቀጠቀጡ ፥ለማሰር የሐገሪቱን ጠቅላይ ሚንስትር ቀጥተኛ ትዕዛዝ መጠበቅ አላስፈለጋቸዉም።አዲስ አበባ የአፍሪቃ መሪዎችን ጉባኤያ ለማተናገድ የትልቅ መሪዋ አለመኖር አላጎላትም።ኢትዮጵያ በደቡብ ሱዳን የነፃነት በአልና በአፍሪቃ ሕብረት ጉባኤ ላይ በአዲሰ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሯና በዉጪ ጉዳይ ሚንስትሯመወከሏ ክብሯን አልቀነሰባትም።የአንጋፋ ዋና መሪዋ ግራ-አጋቢ ጤንነት የዉር ድንብር እያዳፋት፣ እሳቸዉ በሌሉበት ባለችበት መቀጠሏን-ካለመቀጥሏ ቃርጮሽ መሸጎጡ ነዉ ፈተናዉ።እንዴት ላፍታ አብረን እንጠይቅ።


በኢትዮጵያ የቀድሞዉ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ዴቪድ ሺንና የቀድሞዉ የሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ ጦር አዛዥ ዶክተር አረጋዊ በርሔ በአካል መተዋወቅ አለመተዋወቃቸዉን እኛ አናዉቅም።ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዉን ግን ሥልጣን፣ ጊዜና ሥፍራዉ ይራራቅ እንጂ ሁሉቱም በቅርብ ያዉቋቸዋል።

የመለስን መታመም የሰሙት፣ ሥለ ሕመማቸዉና በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ሥለሚያደርሰዉ ተፅዕኖ አስተያየት የሰጡትም ከቋንቋ፣ ቦታ፣ ሠዓታት ልዩነት ባለፍ እኩል ነዉ።«መለስ» አሉ የኢትዮጵያዉን መሪ መጀመሪያ እንደ ፕሬዝዳንት ኋላ እንደ ጠቅላይ ሚንስትር በቅርብ የሚያዉቋቸዉ የቀድሞዉ አሜሪካዊ ዲፕሎማት «መለስ አስቀድመዉ የሚያቅዱ አይነት መሪ ናቸዉ።»

ሺን መለስን በቅርብ ከማወቃቸዉ ከብዙ አመታት በፊት አረጋዊ በርሔ መለስን እንደ አለቃ እያዘዙ፣ እንደ የበላይ እየመሩ፣ እንደ ቀዳማዊ ታጋይ እየመከሩ የነፍጥ ትግልን አብረዋቸዉ ኖረዉበታል።#
ዶክተር አረጋዊ በዚሕ ሁሉ ዘመን በጣም በቅርብ የሚያዉቋቸዉ መለስ ግን ሺን ከገለጧቸዉ መለስ ተቃራኒ ናቸዉ።

የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዘንድሮ ለእረፍት የሚዘጋበት ቀን ተላልፎ ነበር።በልማዱ፣ በምክር ቤቱ ሕግም ምክር ቤቱ የሚዘጋዉ በሚዘጋበት ጊዜ የምክር ቤቱ አባላት በሥራ ዘመናቸዉ ያከናወኑትን ለየመረጣቸዉ ሕዝብ እንዲያስረዱና የሕዝቡን አስተያየት ሰብስበዉ እንዲመለሱ ነዉ።
የምክር ቤቱ የእረፍት ጊዜ ሲራዘም እንደራሴዎቹ ከየመረጣቸዉ ሕዝብ ጋር ለመወያየት የያዙት ቀጠሮ ይታጎላል።ጊዜዉም ያጥራል።

እንደራሴዉ በሕዝብ ከተመረጠ ከመራጩ ጋር የሚገናኝበት ቀጠሮ የታጎለ ወይም ጊዜዉ ያጠረበትን ምክንያት ለመረጠዉ ሕዝብ ማስረዳት ሥላለበት የእረፍት ጊዜዉ የተራዘመበትን ትክክለኛ ምክንያት ማወቅ ግድ በሆነበት ነበር።ምክር ቤቱ በተራዘመዉ የእረፍት ጊዜዉ የቴሌኮም ረቂቅ ሕግንና የመጪዉን ዘመን በጀት አፅድቋል።

የበጀቱን መጠን፣ ምንጩን፣ የሚዉልበን መስክ፣ ማቅረብና ማስረዳት የነበረባቸዉ የሐገሪቱ ጠቅላይ ሚንስትር መሆን ነበረባቸዉ።እንደሚባለዉ በሕዝብ የተመረጡት ጠቅላይ ሚንስትር ከሕዝብ አሰብስበዉ ለሕዝብ የሚያዉሉት በጀት በሕዝብ ተወካዮች ሲፀድቅ አልነበሩም።ጠቅላይ ሚንስትሩ ያልነበሩበት ምክንያት፥ ብቸኛዉ ተቃዋሚ የምክር ቤት አባል አቶ ግርማ ሠይፉ እንደሚሉት አልተነገረም።

የሕዝብ ተወካይ የሚባሉት እንደራሴዎችም-አልጠየቁም።አሜሪካዊዉ የቀድሞ ዲፕሎማት እንዳሉት አስቀድመዉ የሚያቅዱት ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ምክር ቤቱም ሆነ መንግሥታቸዉ የሚፈፅመዉን አስቀድመዉ ያቀዱት ኢሕአዴግን የዘጠና-ዘጠኝ.ሥድስት ከመቶ የድምፅ ድል ሲያጎናፅፉት ሊሆን ይችላል።

ለመለስና በመለስ የረጅም ጊዜ ዕቅድ ምክር ቤት የገቡት ሰዎች ከፓርቲያቸዉ ሌላ የሚያስረዱትም፣ የሚፈርቱም፣ የሚያከብሩትም፣ የሚጠይቃቸዉም ሕዝብ የለም።እነሱም አልጠየቁም።መለስም አልነበሩም።የመለስን መታመም የተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች ዘግበዉበት፥የሕመማቸዉን አይነት፥ ደረጃና የሚታከሙበትን ሥፍራ ሁሉም እንዳሻዉ ተናግሮት ሲያገባድድ ባለፈዉ ሳምንት ሐሙስ የመጀመሪያዉ የመንግሥት ይፋ መግለጫ ከአዲስ አበባ ተሰማ።


#አቶ በረከት ሥምኦን የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ።የመለስ መንግሥት ሥለ መለስ ጤና ለመናገር የዘገየዉ ሺን እንዳሉት መለስ አስቀድመዉ ሥላላቀዱት ይሆን።አቶ ግርማ እንደሚሉት ደግሞ የመንግሥት ባለሥልጣናት ሥለ ጠቅላይ ሚንስትሩ ጤና ለመናገር መዘግየት ብቻ ሳይሆን የሰጡት መረጃም የተሳሳተ ነዉ።


ዶክተር አረጋዊ በርሔም ከመዘግየቱ መሳከሩ ይላሉ።

ዶቸ ቬለ እንደማንኛዉም መገናኛ ዘዴ ሁሉ ሥለመለስ ጤንነት የኢትዮጵያ ባለሥልጣናትና ጉዳዩ የሚመለከታቸዉን ሐገራት ሹማምንት ማብራሪያ እንዲሰጡት በተደጋጋሚ፥ በተለያየ መንገድ ጠይቆ ነበር።ከሚንስትር በረከት መግለጫ ካንድ ቀን በፊት ጠቅላይ ሚንስትሩ ይታከሙበታል የሚባለዉ በብራስልስ-ቤልጂግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኢሜይል የሠጠን መለስ ግን ጠቅላይ ሚንስትሩ ሕክምና ላይ ናቸዉ መባሉን «ሐሰትና ስሕተት» ብሎ ነበር።

ዛሬስ-ሐሰት-ስሕተቱ የትና የማን ነዉ? እዉነቱ ግን መለስ ያኔም-ዛሬም መደበኛ ሥራቸዉ ላይ የሉም።ይሕን በርግጥ ሺን እንደሚሉት አቅደዉት ሊሆን አይችልም።የኢትዮጵያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባለፈዉ አርብ ሐምሌ ስድስት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና የተቃዋሚዉን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ከፍተኛ ባለሥልጣንን ጨምሮ ሃያ-አራት ጋዜጠኛና ፖለቲከኞችን በአሸባሪነት ወንጀል-ከሰባት እስከ እድሜ ልክ በሚደርስ እስራት ቀጥቷቸዋል።

የዚያኑ ዕለት ማታ ፖሊስ የአወሊያንና የሌሎች ቢያንስ ሰወስት የአዲስ አበባ መሳጂዶችን እየረመረመ በየመስጊዶ የነበሩ በሺ የሚቆጠሩ ምዕመናን በአስለቃሽ ጢስ እያፈነ፣ በዱላ እየቀጠቀጠ በየዕሥር ቤቱ አጉሯል።ፓሊስ ባለፈዉ ቅዳሜ ደግሞ ቤተ-እምነቶችን ደፍሮ በርካታ ሙስሊሞችን በጢስ ጋዝ አፍኗል፥ ደብድቧል፥ አስሯልም።

ይሕ ሁሉ አስቀድሞ የማቀድ የመሪነት ልምድና ችሎታ ያላቸዉ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ አስቀድሞዉ አቅደዉ አዘዉም ሊሆን ላይሆንም ይችላል።በዚሕ ሁሉ ጊዜ ግን መለስ መደበኛ ሥራቸዉ ላይ አለመኖሯቸዉ እርግጥ ነዉ።

ዶክተር አረጋዊ በርሔ እንደሚሉት ደግሞ መለስ ለኢትዮጵያ መንግሥት ብቻ ሳይሆን ለታገሉለት ፓርቲም ሁሉም ናቸዉ።


መለስ የሉም ማለት ለኢትዮጵያ ሁሉም የለም ማለት ይሆን? አቶ ግርማ።

በሥልጣን ላይ ላለዉ ገዢ ፓርቲ ለኢሕአዲግ ግን መለስ ሁሉም ናቸዉ በሚለዉ ሐሳብ አቶ ግርማ ይስማማሉ።

የኢትዮጵያ መንግሥት የመለስን መታተመም በይፋ ካመነ-ካለፈዉ ሐሙስ ወዲሕ አንዳድ የሐገሪቱ ባለሥልጣናት የመለስ አለመኖር የመንግሥትን የዕለት ከዕለት ሥራ አያጉልም ባይ ናቸዉ።የገዢዉ ፓርቲ አሠራር-አወቀቃቀርም በነበረበት ይቀጥላል።ዶክተር አረጋዊ በርሔ ይሕን አይቀበሉትም።

ባለፉት ሃያ-አንድ አመታት ኢትዮጵያን የመሩት ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ለረጅም ጊዜ ከመደበኛ ሥራቸዉ ከተለዩ በሐገሪቱ ፖለቲካዊ ሒደት ላይ የሚያደርሰዉ ተፅዕኖ አይኖርም ማለት ያሳስታል።የኢትዮጵያ ፖለቲካ ማለት የተቃዋሚ ፓርቲዎችም እንቅስቃሴ ማለት ነዉ።


ዶክተር አረጋዊ በርሔ፥በይፋ እንደሚታወቀዉ፥ የሐገሪቱ ሕግ እንደሚያዘዉም የሐገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትርና ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም ደሳለኝ ጠቅላይ ሚንስትሩን ተክተዉ ይሠራሉ።እስከ መቼ-አይታወቅም።ነጋሽ መሐመድ ነኝ ቸር ያሰማን።

autor: ludger schadomsky copyright: ludger schadomsky/dw titel: wahlkampf äthiopien 2010 thema:abschlussveranstaltung der regierenden EPRDF im nationalstadium von addis abeba. 30.000 anhänger, die aus allen landesteilen mit bussen herangefahren worden sind, verbreiten siegsstimmung vor dem wahltag sonntag schlagwörter: äthiopien wahl 2010, ethiopia elections 2010,EPRDF, election campaign
የ2002ቱ የምርጫ ዘመቻምስል DW
Karte Äthiopien englisch

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ











ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ