የኢትዮጵያ የፀረ-ሙስና ኮሚሽን
ሐሙስ፣ መስከረም 20 2003ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ የሥነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሙስናን ለመዋጋት «አዲስ» ያለዉን ባለ-አምስት ነጥብ እቅድ ማዉጣቱን አስታወቀ።አምስቱን እቅዶቹን በሚቀጡሉን አምስት አመታት ገቢራዊ እንደሚያደርግም የኮሚሽኑ ባለሥልታናት አስታዉቀዋል።ከእቅዶቹ አንዱ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ሐብትና ንብረት መመዝገብ ነዉ።የአርባ-አምስት ሺሕ ባለሥልጣናት ሐብትና ንብረትን በመጪዉ ሕዳር ይመዘግባል።የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት መብት ጉባኤ በበኩሉ ሐብትና ንብረትን በተመለከተ የሚፈፀሙ በደሎችን እየተከታተለ መሆኑን አስታዉቋል።ጌታቸዉ ተድላ ሀይለጊዮርጊስ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ