1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር መግለጫ

ሐሙስ፣ ኅዳር 9 2014

የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደነገሩት በጦርነቱ ለተጎዳዉ ሕዝብ ርዳታ ለመስጠት የበረራ ፈቃድ የጠየቁ ድርጅቶች ፍቃዱ ተሰጥቷቸዋል። የርዳታዉን መጠንና  ለችግረኛዉ የሚደርስበትን ጊዜ ግን ቃል አቀባዩ አልገለጡም።

https://p.dw.com/p/439VO
Äthiopien Wöchentliche Dina Mufti bei der Pressekonferenz des Ministeriums für auswärtige Angelegenheiten zu aktuellen diplomatischen und geopolitischen Themen
ምስል Solomon Muchie/DW

የዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ጋዜጣዊ መግለጫ

ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ወደ ሚቆጣጠራቸዉ ላሊበላ እና ኮምቦልቻ ከተሞች ርዳታ ለማቅረብ ለሚፈልጉ ድርጅቶች የበረራ ፍቃድ መስጠቱን የኢትዮጵያ መንግስት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደነገሩት በጦርነቱ ለተጎዳዉ ሕዝብ ርዳታ ለመስጠት የበረራ ፈቃድ የጠየቁ ድርጅቶች ፍቃዱ ተሰጥቷቸዋል። የርዳታዉን መጠንና  ለችግረኛዉ የሚደርስበትን ጊዜ ግን ቃል አቀባዩ አልገለጡም። አምባሳደር ዲና በጋዜጣዊ መግለጫዉ የኬንያዉ ፕሬዝደንት ኡሑሩ ኬንያታ በቅርቡ አዲስ አበባ ዉስጥ ከጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አሕመድ ጋር ሥላደረጉት ዉይይት ዝርዝር ማብራሪያ መስጠት አልፈቀዱም።

ሰለሞን ሙጬ 

ነጋሽ መሐመድ

ኂሩት መለሰ