የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር የተላለፈው ውሳኔና አንድምታው
ረቡዕ፣ ነሐሴ 26 2013ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ይረዳል ያለውን በኢኮኖሚ ውስጥ የሚዘዋወረውን የገንዘብ ስርጭት የሚቀንስ ቁጥብ የገንዘብ ፖሊሲን ከዛሬ ነሐሴ 26 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚያደርግ አስታወቀ። ብሔራዊ ባንኩ ግሽበቱን ለመቀነስ ካስተላለፋቸው ውሳኔዎች የባንኮች የመጠባበቂያ ተቀማጭ ምጣኔን በእጥፍ ማሳደግ እና ከብሔራዊ ባንክ የሚበደሩበት ዓመታዊ ወለድ ምጣኔን ማሻሻል ይገኝበታል። ዶይቼ ቬለ ያነጋገራቸው የኢኮኖሚ ባለሙያ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተስተዋለ ያለውን የዋጋ ግሽበት ለመቆጣጠር ከሁሉም ቀዳሚ ግብርናን መደጎም ነው ይላሉ።
ስዩም ጌቱ
ሸዋዬ ለገሠ
ኂሩት መለሰ