1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ቡድን በአፍሪቃ እግር ኳስ ግጥሚያ

ማክሰኞ፣ ጥር 21 2005

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሐያ-ዘጠነኛዉ የአፍሪቃ እግር ኳስ የዋንጫ ግጥሚያ መቀጠል-አለመቀጠሉ ከግማሽ ሠዓት በሕዋላ ከናይጄሪያ ባላጋራዉ ጋር በሚያደርገዉ ግጥሚያ ዉጤት ይወሰናል።

https://p.dw.com/p/17Tl1
Ethiopian football fans in Johansberg DW Amharisch Correspondent Haimanot Turuneh in Johannesburg Schlagworte Haimanot Turuneh , Africa cup Datum 280113 Fotograf Haimanot Turuneh (Amharische Korrespodentin)
ምስል DW/H. Turuneh

ከሰላሳ-ዓመት በሕዋላ ከትልቁ ዉድድር የገባዉ ኢትዮጵያ ቡድን ለሚቀጥለዉ ዙር ለማለፍ ወደ ሜዳ የሚገባዉ ከጠባብ ዕድል ጋር ነዉ።ማሸነፍ ብቻ።ኢትዮጵያዉያን ተጫዋቾች ከዚሕ ቀደም የዛምቢያ ባላጋራቸዉን ሲገጥሙ ያሳዩትን አይነት ያጨዋወት ጥበብ፥ ቅልጥፍና፥ ጥንካሬ እና ከሁሉም በላይ በራስ የመተማመን ብርታን ከደገሙት ኢትዮጵያዉያን ስፖርት አፍቃሪዎችን «ማታ ነዉ ድሌን ሊዘፍኑ» ቢዘጋጁ ይገባቸዋል።ተጨዋቾቹ ባለፈዉ አርብ ከቡርኪና ፋሶ ቡድን ጋር ሲጋጠሙ የነበሩት አይነት ከሆኑ ግን-ተመልካቹ ለትካዜ፥ ተጨዋቾቹ ጓዛቸዉን ለመጠቅለል መዘጋጀት ግድ ነዉ-የሚሆንባቸዉ።ግጥሚያዉን እዚያዉ ደቡብ አፍሪቃ ሆና የምትከታተለዉ ሐይማኖት ጥሩነት  የኢትዮጵያ ቡድን ደጋፊዎችን አነጋግራለች።

ሐይማኖት ጥሩነህ

ነጋሽ መሀመድ

ሂሩት መለሰ