1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ምርጫ ውጤትና የጀርመን መንግስት አስተያየት

ረቡዕ፣ ሰኔ 16 2002

የኢትዮጵያን ጅምር ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለማጠናከር በሐገሪቱ ፖለቲከኞች መካከል ውይይት ማድረግ እንደሚጠቅም አንድ የጀርመን ከፍተኛ ባለሥልጣን አስታወቁ ።

https://p.dw.com/p/O160
ምስል dpa Zentralbild

የጀርመን ውጭ ጉዳዪ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ምክትል ቃል አቀባይ ዛሬ ለዶይቼቬለ እንደገለፁት በቅርቡ የተደረገው ምርጫ ውጤት ያስከተለውን ውዝግብ በተመለከተ ግን መንግስት አቋም የሚይዘው የአውሮጳ ህብረት ታዛቢ ቡድን የመጨረሻ ዘገባ ይፋ ሲሆን ነው ። ቃል አቀባዩን ያነጋገራቸው የዶይቼቬለ የአማርኛ ክፍል ሀላፊ ሉድገር ሻዶምስኪ ነው ። ዘገባውን ልደት አበበ አጠናቅራዋለች ።

ልደት አበበ

አርያም ተክሌ