የኢትዮጵያዉን የተቃዉሞ ሰልፍ በብራስልስ
ዓርብ፣ ጥቅምት 17 2004ማስታወቂያ
ሰልፉን ያዘጋጁት አስተባባሪዎች ከየትኛዉም የፖለቲካ ፓርቲ ጋ ያልተገናኘ እዚያዉ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ተነጋግረዉ በአገር ዉስጥ ይፈጸማል ያሉትን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ለመቃወም የወጡበት እንደሆነም ለብራስልሱ ዘጋቢያችን አስረድተዋል። ሰልፈኞቹ ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ፤ ጋዜጠኞች ከእስር እንዲለቀቁ፣ ከማሳሰብ በተጨማሪ የአዉሮጳ ኅብረት የአቶ መለስ ዜናዊን አስተዳደር መደገፉን እንዲያቆም ጠይቀዋል።
ገበያዉ ንጉሤ
ሸዋዬ ለገሠ
ነጋሽ መሐመድ