1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮዽያ ፍርድ ቤት ውሳኔና የኦነግ ምላሽ

ሐሙስ፣ ሰኔ 3 2002

በ24 የኦሮሞ ነጻነት ግንባር አባላት ላይ ውሳኔ ተሰጠ

https://p.dw.com/p/Nn8u
ምስል AP

በትላንትናው ዕለት የተሰየመው የኢትዮዽያ ፍርድ ቤት ከፍተኛው የዕድሜ ልክ፤ ዝቅተኛው 3ዓመት ተኩል የሆነ ፍርድ አስተላልፍዋል። የኦነግ አባላት ናቸው በተባሉት በእነዚህ ግለሰቦች ላይ ውሳኔው የተላለፈው ህገ ወጥ የሆነ ድርጅት አባል በመሆን በፈጸሙት የሽብር ተግባር 16 ሰዎችን ገድለዋል በሚል እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ገልጸዋል።የኦነግ ምክር ቤት አባልና ቃል አቀባይ ዶክተር በያን አሶባ ለዶቸ ቬሌ እንደገለጹትውሳኔ የተላለፈባቸው ግለሰቦች የኦነግ አባል አይደሉም--የተፈረደባቸውም ኦሮሞ ስለሆኑ ነው-ብለዋል።

መሳይ መኮንን

ነጋሽ መሀመድ