የኢራንና የሐያላኑ ድርድር
ረቡዕ፣ ጥቅምት 6 2006ማስታወቂያ
የኢራን የኑክሌር መርሐ-ግብር የጫረዉን ዉዝግብ ለማስወገድ በኢራንና በሐያላኑ መንግሥታት ተወካዮች መካካል ትናንት ጄኔቭ-ሲዊዘርላንድ የተጀመረዉ ድርድር ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ።የኢራንና አምስት ሲደመር አንድ የተሰኘዉ ቡድን የሚያስተናብራቸዉ ባለሥልጣናት በየፊናቸዉ እንዳስታወቁት ያሁኑ ድርድር ከእስካሁኑ ሁሉ የተሻለ የመግባባት መንፈስ የታየበት ነዉ።ይሁንና በድርድሩ የማካፈሉት እስራኤልና የአሜሪካ ወግ አጥባቂ ፖለቲከኞች በኢራን ላይ የተጣለዉ ማዕቀብ እንዳይላላ ግፊት እያደረጉ መሆናቸዉ ተሰምቷል።ግፊቱ ብልጭ ያለዉን ተስፋ እንዳያጨናጉለዉ ማስጋቱም አልቀረም።የብራስልስ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴን በሥልክ አነጋግሬዋለሁ።
ገበያዉ ንጉሴ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ