1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢራንና የሐያላኑ ድርድር

ረቡዕ፣ ጥቅምት 6 2006

የኢራንና አምስት ሲደመር አንድ የተሰኘዉ ቡድን የሚያስተናብራቸዉ ባለሥልጣናት በየፊናቸዉ እንዳስታወቁት ያሁኑ ድርድር ከእስካሁኑ ሁሉ የተሻለ የመግባባት መንፈስ የታየበት ነዉ።

https://p.dw.com/p/1A1DE
Delegations from Iran and other world powers sit before the start of two days of closed-door nuclear talks at the United Nations offices in Geneva October 15, 2013. Iran will face pressure on Tuesday to propose scaling back its nuclear programme to win relief from crippling sanctions as talks between world powers and Tehran resume after a six-month hiatus. REUTERS/Fabrice Coffrini/Pool (SWITZERLAND - Tags: ENERGY POLITICS)
የዤኔቩ ድርድርምስል Reuters

የኢራን የኑክሌር መርሐ-ግብር የጫረዉን ዉዝግብ ለማስወገድ በኢራንና በሐያላኑ መንግሥታት ተወካዮች መካካል ትናንት ጄኔቭ-ሲዊዘርላንድ የተጀመረዉ ድርድር ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ።የኢራንና አምስት ሲደመር አንድ የተሰኘዉ ቡድን የሚያስተናብራቸዉ ባለሥልጣናት በየፊናቸዉ እንዳስታወቁት ያሁኑ ድርድር ከእስካሁኑ ሁሉ የተሻለ የመግባባት መንፈስ የታየበት ነዉ።ይሁንና በድርድሩ የማካፈሉት እስራኤልና የአሜሪካ ወግ አጥባቂ ፖለቲከኞች በኢራን ላይ የተጣለዉ ማዕቀብ እንዳይላላ ግፊት እያደረጉ መሆናቸዉ ተሰምቷል።ግፊቱ ብልጭ ያለዉን ተስፋ እንዳያጨናጉለዉ ማስጋቱም አልቀረም።የብራስልስ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴን በሥልክ አነጋግሬዋለሁ።

ገበያዉ ንጉሴ

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ