1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ የመጨረሻዉ ንጉሰ ነገሥት

ዓርብ፣ ግንቦት 22 2006

« የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥታዊ መንግሥት ለጀርመን መንግሥት ከፍተኛ እርዳታ አድርጎ ነበር። በዝያን ግዜ እንደሚባለዉ ለጀርመን ወደ 200 ሽ ዶላር ርዳታ ኢትዮጵያ ሰታለች» ይላሉ ዶክተር አስፋዉ ወሰን አስራተ፤

https://p.dw.com/p/1C9fS

ዶ/ር ልጅ አስፋዉ ወሰን አስራተ፤ የአፍሪቃና የመካከለኛዉ ምሥራቅ አማካሪ፤ በጀርመን የታወቁ ደራሲ እና የቱቢንገን ዩንቨርስቲ የክብር ሴናተር ናቸዉ። ዶ/ር ልጅ አስፋዉ ወሰን አስራተ፤ የዛሬ ሶስት ወር ግድም፤ በጀርመንኛ « ዴር ሌትዝተ ካይዘር ፎን አፍሪቃ፤ ማለትም የአፍሪቃ የመጨረሻዉ ንጉሰ ነገሥት» በሚል ስለ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ፤ 415 ገጾች ያሉት፤ ዳጎስ ያለ ታሪክ አዘል መጽሐፍን፤ ለአንባብያን አቅርበዉ፤ በጀርመን የመጽሐፍ ዓለም፤ በሶስት ወር ግዜ ዉስጥ እጅግ ብዙ ከተነበቡ መጻሕፍት መዘርዝር መካከል አንዱ ለመሆን በቅቶአል። በተለያዩ የጀርመን ከተሞች በሚገኙ፤ የተለያዩ ተቋማትና የብዙኃን መገናኛዎች፤ መጽሐፋቸዉ እንዲተርኩ እና የክብር ፊርማቸዉን እንዲያኖሩ የሚጋበዙት ዶክተር ልጅ አስፋውሰን አስራተ፤ ባለፈዉ ሳምንት መጠናቀቅያ ላይ ራድዮ ጣብያችን በሚገኝበት ቦን ከተማ በተዘጋጀላቸዉ የሥነ-ጽሑፍ ፊስቲቫል ምሽት ላይ ተገኝተዉ፤ ስለ ፃፉት መጽሐፋቸዉ እና ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ ሰፊ ማብራርያ ሰጥተዉ፤ በርካቶችን አስደምመዋል፤ በዚሁ የስነ-ፅሁፍ ፊስቲቫል ላይ ተገኝተን ከዶክተር ልጅ አስፋዉ ወሰን አስራተ ጋር ዉይይት አድርገን በዛሪዉ ዝግጅታችን ይዘን ቀርበናል፤

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ