1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ኅብረት የኮሚሽን ምርጫ

ረቡዕ፣ ሰኔ 27 2004

የአፍሪቃ ኅብረትን ኮሚሽን ፕሬዝደንት ለመምረጥ ተከታታይ ዉይይቶች በመካሄድ ላይ ናቸዉ። ከአዉሮጳዉያኑ 2008ዓ,ም ጀምሮ የኮሚሽኑ ፕሬዝደንት የነበሩት ዣን ፒንግን ስፍራ ለመረከብ ደቡብ አፍሪቃ ከፍተኛ ጥረት እያደረገች እንደምትገኝ

https://p.dw.com/p/15RKb
Das neu erbaute Hauptquartier der der Afrikanischen Union (AU) in Addis Abeba, aufgenommen vor der offiziellen Eröffnung am Samstag (28.01.2012). Der 100 Meter hohe Turm mit angrenzendem Konferenzzentrum ist derzeit das höchste Gebäude der äthiopischen Hauptstadt. Hier wird am Sonntag und Montag das 18. Gipfeltreffen der Staatengemeinschaft abgehalten. Nach dreijähriger Bauzeit wurde das 200 Millionen Dollar (152 Millionen Euro) teure Projekt erst kürzlich fertiggestellt. Die Kosten für den vom chinesischen Tongji Design Institut entworfene Bau übernahm komplett die Regierung in Peking. Foto: Carola Frentzen dpa (zu dpa 0231 am 28.01.2012) +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture-alliance/dpa

ዘገባዎች ያመለክታሉ። ኅብረቱ ይህን የኃላፊነት መንበር በፆታ ድልድል የማፈራረቅ መመሪያ ቢኖረዉም፤ የደቡብ አፍሪቃ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይቲ ናኮና ማሻባኔ ለደቡብ አፍሪቃ ሀገሮች የልማት ማኅበረሰብ እንደጠቆሙት ላለፉት 49ዓመታት ይህን አላደረገም። ፉክክር ለበዛበት ለዚህ የኃላፊነት መንበር በመጪዉ ሳምንት የሚጀመረዉ የአፍሪቃ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ እልባት ያገኝለታል ተብሎ ይጠበቃል። ይህ በእንዲህ እንዳለም አዲስ አበባ በሚገኘዉ የኅብረቱ ጽሕፈት ቤት ዲፕሎማቶች በዚሁ ላይ ምክክር ይዘዋል።

ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

ሸዋዬ ለገሠ

ሒሩት መለሠ