1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ መሬትና የለበፀገዉ አለም ሽሚያ

ማክሰኞ፣ የካቲት 17 2001

የበለፀጉት ሐገራት ድንበር ዘለል ኩባንዮችና መንግሥታት ለሙን የአፍሪቃ መሬት በገፍ እየገዙና እየተኮናተሩ የአገሬዉን ሕዝብ ላደገኛ ችግር እያጋለጡት መሆኑን ጉዳዩን ያጠኑ አንድ ጀርመናዊ አስታወቁ።

https://p.dw.com/p/H0WN
ምስል picture-alliance/dpa

እምነትና ፍትሕ የሚለዉን ተቋም የሚመሩት ቮልፍጋንግ ሾኔክ ለጀርመን ምክር ቤት እንደነገሩት በርካታ ኩባንያዮችና መንግሥታት የአፍሪቃን መሬት በግዢም በኮንትራትም ብለዉ እየተቆጣጠሩት ነዉ።እርምጃዉ በዚሕ ከቀጠለ አፍሪቃዉያን ከቀድሞዉ ቅኝ አገዛዝ ዘመን የከፋ ችግር እንደሚገጥማቸዉ ባለሙያዉ ጠቁመዉ ችግሩ ለአዉሮጳም እንደሚተርፍ አስጠንቅቀዋል።የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ሐይለ-ሚካኤል የባለሙያዉን መግለጫ ተከታትሎት ነበር።

Negash Mohammed,Hirut Melesse