1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ሕብረት የሚንስትሮች ሥብሰባ

ረቡዕ፣ ጥር 18 2008

የሚንስትሮቹ ሥብሰባ ዛሬ ሲጀመር የወቅቱ የሕብረቱ የሚንስትሮች ምክር ቤት ሊቀመንበር የዚምባቡዌዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ለባልደረቦቻቸዉ እንደነገሩት ሕብረቱን ለማጠናከር አባል ሐገራት መዋጮቸዉን መክፈል አለባቸዉ

https://p.dw.com/p/1HksP
ምስል F. Batiche/AFP/Getty Images

[No title]

የአፍሪቃ ሕብረት አባል ሐገራት የዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ዛሬ አዲስ አበባ ዉስጥ ተሰብሰበዋል።ሚንስትሮቹ ነገን ጨምሮ ለሁለት ቀን በሚያደርጉት ሥብሰባ የፊታችን ቅዳሜ ለሚጀመረዉ የመሪዎች ጉባኤ የመነጋገሪያ ርዕሶችን ያረቅቃሉ።የሚንስትሮቹ ሥብሰባ ዛሬ ሲጀመር የወቅቱ የሕብረቱ የሚንስትሮች ምክር ቤት ሊቀመንበር የዚምባቡዌዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ለባልደረቦቻቸዉ እንደነገሩት ሕብረቱን ለማጠናከር አባል ሐገራት መዋጮቸዉን መክፈል አለባቸዉ።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ በቅርቡ የናጄሪያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ሆነዉ የተሾሙትን የቀድሞዉ የአፍሪቃ ሕብረት የሠላምና የፀጥታ ኮሚሽነር ራምታ ላማምራን አነጋግሮ ያጠናቀረዉን ዘገባ ልኮልናል።

ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ