1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ህብረት ትምህርት ቤት በመቅዲሾ

ረቡዕ፣ የካቲት 9 2003

ከሶማሊያ መዲና መቅዲሾ የቀድሞ ነዋሪዎች አብዛኛዎቹ ከከተማይቱ ሸሽተው ወጥተዋል ። ያም ሆኖ ልጆች ያሏቸው አንዳንድ ቤተሰቦች እዚያው ይኖራሉ ።

https://p.dw.com/p/R1TI
ምስል picture-alliance / dpa

የሶማሊያን የሽግግር መንግስት የሚደግፈው የአፍሪቃ ህብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል በመዲናይቱ ላሉት ልጆች መደበኛ ትምሕርት የሚሰጥ አንድ ትምሕርት ቤት ከፍቷል ። በዚሁ የአፍሪቃ ህብረት ትምሕርት ቤት የእንግሊዘኛ ቋንቋ ትምሕርት የሚሰጥ ሲሆን እግር ኳስ መጫወትም ይፈቀዳል ። የምዕራብ ጀርመን የቴሌቪዥን ድርጅት ባልደረባ Antje Diekhans በዚሁ ትምህርት ቤት ተገኝታ የተማሪዎቹን ውሎ ተከታትላ ያቀናበራችውን ዘገባ ሂሩት መለሰ አጠናቅራዋለች ። Antje Diekhans ፣

ሂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ