1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአውሮጳ ፖርላማ ልዑካን የኢትዮጵያ ጉብኝት

ሐሙስ፣ መጋቢት 29 2008

የአውሮጳ የሶሻሊስቶችና ዴሞክራቶች አባላት ቡድን ባለፈው ሳምንት አዲስ አበባ ውስጥ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር ተነጋግሮ ነበር ።

https://p.dw.com/p/1IRZ4
Gianni Pittella im Europäischen Parlament Fraktionsvorsitzender der Progressiven Allianz der Sozialisten und Demokraten
ምስል picture-alliance/dpa/D.Aydemir/AA

[No title]



በአውሮጳ ፓርላማ የሶሻሊስቶችና ዴሞክራቶች አባላት ቡድን ያዘጋጀው የአፍሪቃ ሳምንት መርሃ ግብር ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ ብራሰልስ ውስጥ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየተካሄደ ነው። ይኽው ልዩ መርሃ ግብር ፣ ግጭቶችን በማስወገድ በሴቶችና በህጻናት መብቶች በትምህርትና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ዝግጅቶችና ውይይቶች ተካሂደውበታል ። የዚህ መርሃ ግብር አዘጋጅ የአውሮጳ የሶሻሊስቶችና ዴሞክራቶች አባላት ቡድን ባለፈው ሳምንት አዲስ አበባ ውስጥ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር ተነጋግሮ ነበር ። የብራሰልሱ ዘጋቢያችን ገበያው ንጉሴ ስለ መርሃ ግብሩና ቡድኑ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ጋር ስላካሄደው ውይት ይዘት የቡድኑን ፕሬዝዳንት አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል ።

ገበያው ንጉሴ

ኂሩት መለሰ

አዜብ ታደሰ