1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአውሮጳ ህብረት የው/ጉዳይ ክፍል ምላሽ ለሂውመን ራይትስ ዎች ደብዳቤ

ማክሰኞ፣ መጋቢት 19 2009

የመብት ተሟጋቹ ድርጅት፣ «ሂውመን ራይትስ ዎች» የአውሮጳ ህብረት የውጭ ጉዳይ ተጠሪ ፌዴሪካ ሞጌሪኒን የቅርብ ጊዜ የኢትዮጵያ ጉብኝትን ተከተሎ አንድ የወቀሳ ደብዳቤ ጽፏል።

https://p.dw.com/p/2a9wl
Vertreterin der Europäischen Union für Außen- und Sicherheitspolitik Federica Mogherini
ምስል DW

ድርጅቱ በደብዳቤዉ የኅብረቱ የውጭ ጉዳይ ተጠሪ ሞጌሪኒ ከጉብኝታቸው በኋላ ባወጡት በመግለጫቸዉ በኢትዮጵያ ስለሚታየዉ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት አልጠቀሱም በማለት ወቅሷል። ይህ ይፋዊ መግለጫቸዉ ከሀገሪቱ ባለስልጣናት ጋር ስላካሄዱት የሁለትዮሽ ግንኙነት ከመዘርዘር ዉጭ፤ ስለአስቸኳዩ ጊዜ አዋጁም ሆነ በእስር ላይ ስለሚገኙ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፣ ተቃዋሚ ሰልፈኞች እና ጋዜጠኞች ጉዳይ እንዳላነሱም «ሂውመን ራይትስ ዎች»  ዘርዝሯል። 

ገበያው ንጉሤ

አርያም ተክሌ

ሸዋዬ ለገሠ