1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአዉሮጳ እና አፍሪቃ ግንኙነት

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 24 2010

የአፍሪቃ እና የአዉሮጳ ግንኙነት ረዥም ዘመን አስቆጥሯል።  አፍሪቃ በአዉሮጳ ሃገራት ቅኝ ከመገዛት ነፃ ከወጣ በኋላ የሁለቱ አህጉራት ግንኙነት የቅኝ ገዢ እና ተገዢ አይነት ሆኖ ቆይቷል። በአብዛኛዉም የእርዳታ ሰጪና ተቀባይነት ትስስሩ ይጎላል።

https://p.dw.com/p/2qCqs
Efenbeinküste EU-Afrika-Gipfel in Abidjan Gruppenbild
ምስል picture-alliance/AP Photo/G. V. Wijngaert

ከቅኝ ገዢ እና ተገዢነት ግንኙነት እየተለወጠ ነዉ፤

ከቀዝቃዛዉ ጦርነት በኋላ የምሥራቁ ጎራ ሲፈራርስ፤ አፍሪቃ ከአዉሮጳ ጋር ለሚኖራት ትስስር ዴሞክራሲ ማስፈን፤ የሰብአዊ መብቶችን ማክበር፣ እንዲሁም የነጻ ገበያ መርህ እና የመሳሰሉት ፅንሰ ሃሳቦች ከምዕራቡ ዓለም ጋር ለሚደረጉ ግንኙነቶች እንደመሠረት ይወሰዳሉ በሚል እስካሁን ይነገራል። በመልካም አስተዳደር እና ተያያዥ ምክንያቶች ሰበብ ከአፍሪቃ ተሰዳጆች መበርከታቸዉ፣ እንዲሁም የሽብር እንቅስቃሴ ያሰጋዉ አዉሮጳ ባለፈዉ ጎርጎሪዮሳዊ ዓመት በቅኝ ገዢነት በቅርብ ከሚያዉቃት አፍሪቃ ጋር የተለየ ጉድኝት እንደሚያሻዉ በማመላከት አዲስ ትብብር በሁለቱ አህጉሮች መካከል መሥርቷል። የትራምፕ አስተዳደር ያፈነገጠ አካሄድ፣ የቻይና በአፍሪቃ እንደልብ መንቀሳቀስ፤ የብሪታኒያ ከኅብረቱ መዉጣት ለአዉሮጳ በቅርብ ርቀት ከምትገኘዉ ከአፍሪቃ የተሻለ ተጓዳኝ እንደሌለዉ ያመላከተ መስሏል። በዘንድሮዉ አዲስ ዓመትስ የሁለቱ ግንኙነት እንዴት ይቀጥል ይሆን? የዕለቱ አዉሮጳ እና ጀርመን መሰናዶ የአፍሪቃ እና አዉሮጳን ግንኙነት ይቃኛል። 

ገበያዉ ንጉሤ

ሸዋዬ ለገሠ