1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአዉሮጳ ሕብረት ዉሳኔ እና ሒዝቡላሕ

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 16 2005

ሒዝቡባላሕ ግን ፍረጃዉን «የአሜሪካና የፅዮናዉያን ሴራ» በማለት ሲያወግዘዉ፥ የሊባኖስ መንግሥት ደግሞ ለሊባኖስ «ተጨማሪ ችግር ፈጣሪ» በማለት ተቃዉሞታል።የፖለቲካ ተንታኞችም የአዉሮጳ ሕብረት ዉሳኔን ገቢራዊነት ይጠራጠራሉ

https://p.dw.com/p/19DG5
epa03717034 Supporters of Hezbollah listen to the Secretary General of Hezbollah Sayyed Hassan Nasrallah, speaking on a giant screen via video link from an undisclosed location, during a rally to mark the Resistance and Liberation Day, in the village of Mashghara, in the eastern Bekaa valley, Lebanon, 25 May 2013. The Liberation Day commemorates the Israeli army's withdrawal from south Lebanon in May 2000 following 22 years of occupation. EPA/WAEL HAMZEH pixel
ምስል picture-alliance/dpa

የአዉሮጳ ሕብረት የሊባኖሱን ደፈጣ ተዋጊ ቡድን ሒዝቡላሕን በአሸባሪነት መፈረጁን እራሱ ሒዝቡላሕና የሊባኖስ መንግሥት አወገዙት።ሕብረቱ፥ እስራኤል በሐይል የያዘችዉን የሊባኖስ ግዛት ነፃ ለማዉጣት የሚፋለመዉን ቡድን በአሸባሪነት የፈረጀዉ ቡድኑ በሶሪያዉ ጦርነት ጣልቃ ገብቷል፥ እስራኤላዊ ሐገር ጎብኚዎችን አስገድሏል በሚል ነዉ።ሒዝቡባላሕ ግን ፍረጃዉን «የአሜሪካና የፅዮናዉያን ሴራ» በማለት ሲያወግዘዉ፥ የሊባኖስ መንግሥት ደግሞ ለሊባኖስ «ተጨማሪ ችግር ፈጣሪ» በማለት ተቃዉሞታል።የፖለቲካ ተንታኞችም የአዉሮጳ ሕብረት ዉሳኔን ገቢራዊነት ይጠራጠራሉ።ሥለ ዉሳኔዉ እና አፀፋዉ የብራስልስ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።

ገበያዉ ንጉሴ

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ