1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መራዘም

ሐሙስ፣ መጋቢት 21 2009

የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 21ኛ መደበኛ ስብሰባ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለሚቀጥሉት አራት ወራት እንዲራዘም ወስነ። ምክር ቤቱ የአዋጁን መራዘም ያፀደቀው ስለ መራዘሙ አስፈላጊነት ከኮማንድ ፖስቱ ሃላፊ እና የመከላከያ ሚንስትርአቶ ሲራጅ ፈጌሳ የቀረበለትን ማብራሪያ ካዳመጠ በኋላ ነው ።

https://p.dw.com/p/2aMIP
Äthiopien | Parlament
ምስል DW/Y. G. Egziabher

Beri AA (Ethiopian parliament extended the state of emergency) - MP3-Stereo

 አቶ ሲራጅ ፈጌሳን  አዋጁ እንዲራዘም የተፈለገው ባለፉት ስድስት ወራት በመላ ሀገሪቱ የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም እና መረጋጋት ወደ ማይቀለበስበት ደረጃ ለማድረስ ነው ማለታቸው ተዘግቧል ።በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ለአንድ ዓመት ገደማ ፀረ መንግሥት ተቃውሞ ከተካሄደ በኋላ ነበር ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ባለፈው መስከረም 29 ፣ 2009 ዓም የአስቸኳዩን ጊዜ ያወጁት። በመብት ተሟጋች ድርጅቶች መሰረት፣ በነዚህ ተቃውሞ ወቅት የፀጥታ ኃይላት በወሰዱት የኃይል እርምጃ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተገድለዋል። የተቃዋሚ ፓርቲዎች መንግሥት አዋጁን በተለይ፣ በገጠሩ አካባቢ ያሉትን አባሎቻቸውን እና ስራቸውን ለማፈን እየተጠቀመበት ነው ሲሉ ወቅሰዋል። አዋጁ መራዘሙ ሀገሪቱ የምትገኝበትን አደገኛ ሁኔታ እንደሚያሳይ ዶይቸ ቬለ ያነጋገራቸው ተቃዋሚው የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ መንበር አቶ የሺዋስ አሰፋ ለዶይቸ ቬለ ገልጸዋል።

አርያም ተክሌ
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ 
ሸዋዬ ለገሠ