የአሜሪካንና የኢራን ፕሬዝዳንቶች ንግግር
ሐሙስ፣ መስከረም 16 2006ማስታወቂያ
የዩንይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ለተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ያደረጉትን ንግግር ኢራን አወደሰች ።የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እንዳሉት የኦባማ ንግግር ለዘብ ያለና ለኢራንም አክብሮት የሰጠ ነበር ። እንደ ምክትል ሚኒስትሩ የዓለም ኃያላን መንግሥታት በህጉ መሠረት የኢራን የኒዩክልየር መብት እስካከበሩ ድረስ ለኒዩክልየር ውዝግቡ መፍትሄ ማግኘቱ አዳጋች አይሆንም ። ኦባማ ለተመድ 68 ተኛ ጠቅላላ ጉባኤ ባሰሙት ንግግር ዋሽንግተን ከዚህ ቀደም ለፈፀመቻቸው ስህተቶች ዕውቅና በመስጠታቸው በመገናኛ ብዜሃን ተወድሰዋል ። የዋሽንግተን ዲሲው ወኪላችን
አበበ ፈለቀ ኦባማንና የኢራኑን ፕሬዝዳንት ለጠቅላላ ጉባኤው ያሰሙት ንግግር ላይ ያተኮረ ዘገባ አጠናቅሯል
አበበ ፈለቀ
ሂሩት መለሰ
ተክሌ የኋላ