1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአማራ እና ኦሮሚያ የፀጥታ ኃላፊዎች መግለጫ

ሐሙስ፣ መጋቢት 19 2011

በአማራንና በኦሮሞ ህዝቦች መካከል ሊያጋጭ የሚችል ምንም ነገር እንደሌለ የሁለቱም ክልሎች የፀጥታ ቢሮ ኃላፊዎች አመለከቱ። ሆኖም ግን ኃላፊዎቹ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ “የፖለቲካ ደላላዎች” ያሏቸው ወገኖች የሁለቱን ህዝቦች አንድነት ለመናድ ሌት ተቀን ይሠራሉ ብለዋል።

https://p.dw.com/p/3FqMp
Peace &Security heads of Amhara and Oromia regions
ምስል DW

«በሁለቱ ሕዝቦች መካከል ሊያጋጭ የሚችል ምንም ነገር የለም»

በአማራና አሮሚያ አዋሳኝ አንዳንድ አካባቢዎች፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በአዲስ አበባ የባለቤትነት ጉዳይ ላይ የሁለቱንም ህዝቦች ሰላምና አንድነት የሚፈታተኑ ሁኔታዎች ይታያሉ፡፡ በየጊዜው የሚነሱ የሰላም ጠንቆችን በዘላቂነት ለመፍታት ሚያስችል ውይይት በሁለቱ የፀጥታ ቢሮ ከፍተኛ ኃላፊዎች መካከል ትናንትና በባህር ዳር ከተማ ተካሂዷል፡፡ የውይይቱን አስፈላጊነትና የተደረሰበትን ድምዳሜ አስመልክቶ ዛሬ የአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ከፍተኛ የፀጥታ ኃላፊዎች ለመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ከስፍራው ዘሃቢያችን ዓለምነው መኮንን ዝርዝሩን ልኮልናል።

ዓለምነው መኮንን

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ