1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ኤኮኖሚ

የኖትር ዳም ቃጠሎ

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 8 2011

የጀርመኑ ፕሬዝደንት ፍራንክ ቫልተር-ሻትይን ማየር «የአዉሮጳ መለያ» ያሉትን ካቲድራል ለመጠገን የጀርመንና የመለዉ አዉሮጳ ሕዝብ እርዳታ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።በጥንታዊ ሥነ-ሕንፃ ጥበብ የታወቁት የግሪክና የቼክ መንግሥታት ባለሙያዎች ለመላክ ዝግጁ መሆናቸዉን አስታዉቀዋል

https://p.dw.com/p/3Gu3c
Frankreich Brand Notre Dame
ምስል picture-alliance/Yonhap news agency

የኖትር ዳም ቃጠሎ

ትናንት በእሳት የጋየዉን የፓሪሱን የኖትር ዳም ካቲድራልን መልሶ ለመጠገን የሐገራት መሪዎች፣ድርጅቶችና ኩባንዮች የሞራል፤የሙያና የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ እየተረባረቡ ነዉ።የጀርመኑ ፕሬዝደንት ፍራንክ ቫልተር-ሻትይን ማየር «የአዉሮጳ መለያ» ያሉትን ካቲድራል ለመጠገን የጀርመንና የመለዉ አዉሮጳ ሕዝብ እርዳታ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።በጥንታዊ ሥነ-ሕንፃ ጥበብ የታወቁት የግሪክና የቼክ መንግሥታት ባለሙያዎች ለመላክ ዝግጁ መሆናቸዉን አስታዉቀዋል።የፈረንሳይ ቱጃሮች ቤርናር አርኖ እና ፍራንሷ ፒኖ 300 ሚሊዮን ዩሮ፣ የፈረንሳዩ የነዳጅ ኩባንያ ቶታል 100 ሚሊዮን፣የፈረንሳዩ የመዋቢያዎች አምራች ሎ ርየል 100 ሚሊዮን ዩሮ ለመስጠት ቃል ገብተዋል።ሌሎችም እርዳታ መስጠታቸዉን እንደቀጠሉ ነዉ።

ሐይማኖት ጥሩነሕ 

ነጋሽ መሐመድ

ማንተጋፍቶት ስለሺ