የኑክሌርና የኑክሌር ዝቃጭ ሥጋት ለአፍሪቃ
ረቡዕ፣ ኅዳር 1 2003ማስታወቂያ
የአፍሪቃ ሕብረት አባል ሐገራት አፍሪቃ ዉስጥ የኑክሌር ጦር መሳሪያ እንዳይመረትና የኑክሌር ዝቃኝ እንዳይጣል የሚያግደዉን የሕብረቱን ዉል እንዲያከብሩ ሕብረቱ ጠየቀ።ሰሞኑን አዲስ አበባ ዉስጥ በጉዳዩ ላይ የተነጋገረዉ የሕብረቱ ስብሰባ የኑክሌርን አደጋ የሚከላከልና ኑክሌር ለሰላማዊ አገልግሎት የሚዉልበትን ብልሐት የሚያፈላልግ ኮሚሽን ሰይሟልም።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ እንደዘገበዉ የአፍሪቃ ሕብረት አባላት የኑክሌር አደጋን ለመከለከልና የኑክሌር ሐይልን ለሰላማዊ አገልግሎት ለማዋል የፔሊንዳብራ ዉል የተሰኘዉን ስምምነት ከፈረሙ አስራ-ሰወስት አመት አለፋቸዉ።
ጌታቸዉ ተድላ
ነጋሽ መሐመድ
ሒሩት መለሰ