የኅብረተሰብ ፀጥታ እና ደህንነት ስጋት በባሕር ዳር
ማክሰኞ፣ ግንቦት 20 2011ማስታወቂያ
በባሕር ዳር ከተማ ዝርፊያ፣ ወከባና ስርቆት ነዋሪዎችን እያማረረ ነው፡፡ ሴቶች የእጅ ስልካቸውን እንደሚነጠቁ ፣ ጌጣግጥ አድርገውም ከተማ መውጣት እንደተቸገሩ ይናገራሉ፡፡ ስለሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎችም እንዲሁ መታፈን እና ገንዘብ መዘረፍ የከተማዋ ነዋሪዎች በየጊዜው የሚያሰሙት አቤቱታ ነው፡፡ ከሰሞኑም በድርጊቱ የተጠረጠሩ በቁጥጥር ሥር የመዋላቸው ጉዳይ መሰማቱን ከባሕር ዳር ዘጋቢያችን ዓለምነው መኮንን የላከልን ዘገባ ያስረዳል።
ዓለምነው መኮንን
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ