1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የተባባሰዉ የሰብአዊ መብት ጥሰት በኢትዮጵያ

ረቡዕ፣ ግንቦት 3 2014

ኢሰመኮ ዛሬ ለተወካዮች ምክር ቤት የፍትሕና የዴሞክራሲ ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበዉ የ10 ወር ዘገባዉ እንዳለዉ በየጊዜዉ በሚያገረሹ ግጭቶች ምክንያት የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እየጨመረ፣ ተጠያቂነትና የሕግ የበላይነት እየላላ ነዉ።

https://p.dw.com/p/4B8tK
Deutscher Afrika Preis 2021 - Daniel Bekele
ምስል Deutsche Afrika Stiftung

«ምክር ቤቱ አስፈፃሚዉን አካል መከታተል አለበት» አሰመኮ

 የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሐገሪቱ ዉስጥ እየከፋ የመጣዉን የሰብአዊ መብት ጥሰት ለመከላከል እንዲጥርና መንግሥትን እንዲቆጣጠር የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጠየቀ።ኢሰመኮ ዛሬ ለተወካዮች ምክር ቤት የፍትሕና የዴሞክራሲ ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበዉ የ10 ወር  ዘገባዉ እንዳለዉ በየጊዜዉ በሚያገረሹ ግጭቶች ምክንያት የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እየጨመረ፣ ተጠያቂነትና የሕግ የበላይነት እየላላ ነዉ። ኮሚሽኑ አክሎ እንዳለዉ የመንግሥት የፀጥታ አካላት ከፍርድ ቤት ዉሳኔ ውጪ የሚፈፀምሙት ግድያ፣ ከመጠን ያለፈ የኃይል እርምጃ፣ የዘፈቀደ እሥር እና የፍርድ ቤት ትእዛዝ አለመከበር አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።ምክር ቤቱ ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብሏልም-ኮሚሽኑ።

ሰለሞን ሙጪ 

ነጋሽ መሐመድ

ማንተጋፍቶት ስለሺ