1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቦምብ ፍንዳታ በሶማሊያ

ማክሰኞ፣ ኅዳር 10 2006

ዛሬ በማዕከላዊ ሶማሊያ በለድዌይን ከተማ ውስጥ በኣንድ ፖሊስ ጣቢያ ላይ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ ከ10 ሰዎች በላይ ተገድለው በርካቶች መቄሰላቸው ተሰማ። በመኪና ላሊ የተጠመደ ቦምብ መፈንዳቱን ተከትሎ ታጣቂዎችም ተኩስ ከፍተው ለማምለጥ የሞከሩ ፖሊሶችን ሲገድሉ ማየታቸውን የዓይን እማኞች ተናግሯል።

https://p.dw.com/p/1AKyh
outside the Maka Al-Mukarama hotel in Somalia's capital Mogadishu, November 8, 2013. A suspected car bomb attack outside a popular hotel in the Somali capital on Friday evening killed at least six people and left the area covered with blood and burning vehicles, a senior police officer said. REUTERS/Feisal Omar (SOMALIA - Tags: CIVIL UNREST CRIME LAW)
ምስል Reuters

ለጥቃቱም ከኣልቃኢዳ ጋር ቁርኝት እንዳለው የሚነገርለት ጽንፈኛ ቡድን ኣልሸባብ ሀላፊነት ወስዷል።

ጃፈር ዓሊ

የከተማይቱ በለድዌይን የፖሊስ ዋና ኣዛዥ ኮ/ል አብዱልቃዲር አሊን የጠቀሱ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት የዛሬው ፍንዳታ ድንገተኛ እና ከባድም ነው የነበረው። ድንገተኛ ሲባል ኮ/ሉ እንደሚሉት የውጪ ጥበቃ መላላት ብቻም ሳይሆን ኣዛዦች እንደዋዛ በማይረባ ግርግዳ ውስጥ በተሰባሰቡበት ኣጋጣሚ ነበር ፍንዳታው የደረሰው። ነገር ግን ከባድ ከማለት ያለፈ ኮ/ል አብዱልቃዲር የሟቾችን ቁጥርም ሆነ የደረሰውን ኪሳራ ከመግለጽ ተቆጥቧል። ሁኔታው ብዙም ሳይቆይ ግን በቁጥጥር ስር መዋሉም ተገልጿል።

የዓይን እማኞች እንደሚሉት ኣንድ በከፍተኛ ፍጥነት የሚከንፍ ኣሮጌ መኪና መቶ ከበለድዌይን ፖሊስ ጣቢያ የጊቢ በር ጋር ተጋጨና በርግዶ ገባ። ወዲያውኑ ፊት ለፊት ካለው የጣቢያው ግርግዳ ጋር ከመላተሙ ከፍተኛ ፍንዳታ ደረሰ። ፍንዳታውን ተከትሎም በመተረየስ ጠመንጃ የታጠቁ ተዋጊዎች ከየአቅጣጫው ወደ ጣቢያው መተኮስ ጀመሩ። በፍንዳታው ተደናግጠው ለማምለጥ የሚርበተበቱ ፖሊሶችንም ይገድሉ ነበር ብሏል እማኞች።

ከፍንዳታው በኃላም በርካታ ኣስክሬኖች እየተጎተቱ ወደ ኣንድ ስፍራ ሲከማቹ ኣይተናል የሚሉት የዓይን እማኞች በርካታ ቁስለኞችም ደም እየዘሩ ሲወጡ ማየታቸውን ለዜና ሰዎች ነግሯል። ለጥቃቱም ኣልሸባብ ኃላፊነቱን ወስዷል። ቁስለኞችን ሳይጨምር የሟቾቹ ቁጥርም የጸጥታ ጥናት ተቐም ባልደረባ የሆኑት ሚ/ር ኣንድሩስ አሶማዋ እንደሚሉት ከ 10 እስከ 14 ይገመታል።

«በትክክል ምን ያህል ሰዎች እንደተገደሉ እርግጠኛ ኣይደለንም። የሆነ ሆኖ ግን አ 10 እስከ 14 ሰዎች ሳይሞቱ እንዳልቀረ እገምታለሁ። እንደምታውቁት ጥቃቱ የደረሰው በፖሊስ ጣቢያ ላይ ነው። ጣቢያው ደግሞ የኣፍሪካ ህብረት ጦርም ማዕከል ነው። የጂቡቲ ጦር የሚገኝበት። እናም አደጋው ያንን የኣፍሪካ ህብረት ማዕከል ዒላማ ያደረገ ነው። ኣፈጻጸሙንም ብንመለከት መጀመሪያ በመኪና የተጠመደ ቦምብ እንዲፈነዳ ተደረገ። ቀጥሎም የጠመንጃ ተኩስ እንዲከተል ተደረገ። ይሔ ኣሁን ኣልሸባብ የሚጠቀምበት የጥቃት ዘዴ ነው።»

A young Alshabab soldier prepares to join fighting between Alshabab and Ethiopian forces near the presidential palace in Mogadishu, Somalia on 12, January 2009. Islamic fighters launched heavy attacks on two Ethiopian bases on the eve of Ethiopian expected withdrawal from Somalia. EPA/BADRI MEDIA +++(c) dpa - Report+++
ምስል picture-alliance/dpa

በኢትዮጵያ ድንበር ኣቅራቢያ የምትገኘው የበለድዌይን ከተማ ከዋና ከተማይቱ ሞቃዲሾ በስተ ሰሜን 300 ኪ ሜ ላይ ስትገኝ በአካባቢው ዋና ስልታዊ ከተማ እንደሆነች ይነገርላታል። ባለፈው ወር በኣንድ የኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በምትገኝ ከተማ በኣንድ ምግብ ቤት ውስጥ ኣንድ ኣጥፍቶ ጠፊ ባፈነዳው ቦምብ 15 ሰዎች መገደላቸው የሚታወስ ሲሆን በወቅቱም ለጥቃቱ ኣልሸባብ ኃላፊነት መውሰዱ ኣይዘነጋም።

Photo taken September 22, 2012 shows AU soldiers from Uganda looking at some of the weapons recovered from members of Somalia's Al-Qaeda-linked Shebab after they gave themselves up to African Union Mission in Somalia (AMISOM) forces in Garsale, some 10km from the town of Jowhar, 80km north of the capital Mogadishu. Over 200 militants disengaged following in-fighting between militants in the region in which eight supporters of Shabaab were killed, including two senior commanders. The former fighters were peacefully taken into AMISOM's protection handing in over 80 weapons in the process, in a further indication that the once-feared militant group is now divided and being defeated across Somalia. Deputy Force Commander of AMISOM Operations, Brigadier Michael Ondoga said a number of militants have contacted the AU force indicating their wish to cease fighting and that they their safety is assured if they give themselves up peacefully to AMISOM forces. AFP PHOTO/ MOHAMED ABDIWAHAB (Photo credit should read Mohamed Abdiwahab/AFP/GettyImages)
ምስል Mohamed Abdiwahab/AFP/Getty Images

ምግብ ቤቱ የሶማሊያው መንግስት ደጋፊዎችን ጨምሮ የኣፍሪካ ህብረት የሶማሊያ ተልዕኮ ጦር አሚሶም እና የኢትዮጵያ ወታደሮች የሚያዘወትሩበት ነው ያለው አልሸባብ ኢላማውም በከተማይቱ የመሸጉ የኢትዮጵያ ወታደሮች መሆናቸውን መግለጹ ይታወቃል።

በሶማሊያ ያለው የኢትዮጵያ ጦር በዚያች ኣገር ካለው የኣፍሪካ ህብረት በምህጻሩ AMISOM ጋር ሊቀላቀል መወሰኑም ታውቐል። ኣፈጻጸሙ ግን አምባሳደር ዲና ሙፍቲ እንደሚሉት በሂደት ነው ተብሏል።

ሞቃዶሾን ጨምሮ ከደቡባዊቷ የወደብ ከተማ ኪስማዮ ጭምር ተገፍቶ የወጣው ኣልሸባብ ኣሁንም ቢሆን ግን በደቡብ ሶማሊያ ሁሪያውን ሁሉ እንደሚቆጣጠrw ይታወቃል።

ጃፈር ዓሊ

ሸዋዬ ለገሠ