1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የብሪታንያ ፖለቲካዊ ቀዉስ

ሐሙስ፣ ነሐሴ 30 2011

የጠቅላይ ሚንስትርነቱን ስልጣን ባለፈዉ ሐምሌ የያዙት ቀኝ አክራሪዉ ፖለቲከኛ ቦሪስ ጆንሰን ከአዉሮጳ ሕብረት ስምምነት ዉጪ ሐገራቸዉን ከሕብረቱ አባልነት ለማስወጣት የሸረቡት ሴራ እራሳቸዉን መልሶ እያዳጣ፣እያሟላጣቸዉ ነዉ

https://p.dw.com/p/3P6hz
Brexit Debatte im britischen Unterhaus
ምስል picture-alliance/empics/House of Commons

የብሪታንያ ፖለቲከኞች ማብቂያ የለሽ ዉዝግብ

ብሪታንያ ከአዉሮጳ ሕብረት አባልነት የምትወጣበት ሥልትና ጊዜ የሐገሪቱን ፖለቲከኞች አሁንም እንዳወዛገበ ነዉ።የጠቅላይ ሚንስትርነቱን ስልጣን ባለፈዉ ሐምሌ የያዙት ቀኝ አክራሪዉ ፖለቲከኛ ቦሪስ ጆንሰን ከአዉሮጳ ሕብረት ስምምነት ዉጪ ሐገራቸዉን ከሕብረቱ አባልነት ለማስወጣት የሸረቡት ሴራ እራሳቸዉን መልሶ እያዳጣ፣እያሟላጣቸዉ ነዉ።ጠቅላይ ሚንስትሩ እንዲዘጋ በሐገሪቱ ንግሥት ያስወሰኑበት የሐገሪቱ ምክር ቤት፣ ብሪታንያ ከምክር ቤቱ ይሁንታና ዕዉቅና ዉጪ ከሕብረቱ አባልነት እንዳትወጣ አግዷል።ጠቅላይ ሚንስትሩ ጥቅምት መጀመሪያ ላይ አጠቃላይ ምርጫ እንዲደረግ ያወጁትንም ዕቅድ ምክር ቤቱ ዉድቅ አድርጎታል።

 ድልነሳ ጌታነሕ 

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሰ