1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቡድን ስምንት ጉባኤ

ሐሙስ፣ ግንቦት 18 2003

የቡድን ስምንት ጉባኤ ዛሬ በፈረንሳይ ዶቪል ተጀመረ።

https://p.dw.com/p/RQCi
ምስል dapd

ዩናይትድ ስቴትስ፤ ካናዳ፤ ብሪታንያ፤ ፈረንሳይ፤ ጀርመን፤ ጣሊያን፤ ጃፓን እና ሩሲያን ያካተተዉ ይህ ቡንድ በዚህ ወቅት ስብሰባዉ፤ በአረብ ሀገራት የተቀጣጠለዉን አብዮት እና በጃፓን ከባድ የመሬት ነዉጥ በፉኩሺማ የኒኩሊየር ኃይል ማመንጫ ላይ ያስከተለዉ አደጋ ላይ ትኩረቱን በማድረግ ይነጋገራል። የጉባኤዉ አስተናጋጅ የፈረንሳይ ፕሬዝደንት ኒኮላስ ሳርኮዚ ለቱኒዚያና ለግብፅ የሚደረገዉን ድጋፍ እንደሚያጸድቁ ሲጠበቅ፤ ጉባኤዉ ከመጀመሩ አስቀድመዉ የጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል ቡድን ስምንት በሰሜን አፍሪቃ የምጣኔ ሃብት ልማት የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያደርግ ጥሪ አድርገዋል።

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ