1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የበማድመጥ መማር ዝግጅት በኢትዮጵያ

ዓርብ፣ ጥቅምት 3 2004

በማድመጥ መማር በሚል ርዕስ ዘውትር ዓርብ ከዶይቸ ቬለ ራዲዮ የሚቀርብላችሁ የሬዲዮ ጭውውት አዳዲስ ክፍሎች ላለፉት ሳምንታት በአዲስ አበባ ሲቀረፁ ሰንብተዋል።

https://p.dw.com/p/Rqfl
ምስል DW
እንደ እኢአ ከ 2008 ጀምሮ ከዶይቸ ቬለ ራዲዮ በተለያዩ ቋንቋዎች ተተርጉሞ የሚቀርበው የበማድመጥ መማር ዝግጅት ነው። ለ4ኛ ጊዜ ይሄው የሬዲዮ ጭውውት በአዲስ አበባ እየተቀረፀ ይገኛል። የጭውውቱ ዳሬክተርና የዶይቼ ቬለ ባልደረባ ማንተጋፍቶት ስለሺ ስለ ስራው ሂደት፤ እንዲሁም ሁለት በጭውውቱ የተሳተፉ ተዋንያንን ልደት አበበ አነጋግራቸዋለች። የበማድመጥ መማር ዝግጅት ከዚህ ቀደም በተለያዩ ትምህርታዊ ርዕሶች ላይ ያተኮሩ የራዲዮ ጭውውቶቹን ሲያስተላልፍ ቆይቷል። አሁንስ በምን ላይ ነው ያተኮረው?ከዝግጅቱ ያገኙታል። ልደት አበበ